በገጣሚዋና በህክምና ባለሙያዋ ዶ/ር አበባ የሺጥላ የተሰናዳውና 66 ያህል ግጥሞችን የያዘው “እግዜር ቅኔ አማረው” የተሰኘው የግጥም ስብስብ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡
በመፅሐፉ ውስጥ የተካተቱ ግጥሞች በርካታ ማህበራዊ ርዕስ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ፍሬያማ ግጥሞች ስለመሆናቸው መፅሐፉን የማንበብ ዕድል የገጠማቸው ግለሰቦች ገልፀዋል፡፡ ዶ/ር አበባ የሺጥላ ከውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ሀኪምነቷ ባሻገር እጅግ ጠንካራና በተለያዩ ማህራዊ ጉዳዮችም ንቁ ተሳትፎ ያላትና የተዋጣላት ገጣሚ እንደሆነችም ለማወቅ ተችሏል፡፡
“እግዜር ቅኔ አማረው” የግጥም ስብስብ መፅፍ በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን በ102 ገጽ ተቀንብቦ በ150 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና