Saturday, 11 June 2022 19:59

የፅጌረዳ ተክልና ቁልቋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ከዕለታት አንድ ቀን፣ ራቅ ባለ በረሃ ላይ በውበቷ እጅጉን የምትኮራና የምትመካ አንድ የፅጌረዳ አበባ ነበረች። እሷን ክፉኛ የሚያማርራት ብቸኛ ነገር፣ ከአስቀያሚ የቁልቋል ተክል አጠገብ መብቀሏ ነበር።
ውቢቷ ፅጌረዳ በየቀኑ ቁልቋሏን በንቀት ስትሰድብና ስታሾፍበት ነው የምትውለው፡፡ ቁልቋሉ ግን ትንፍሽ ብሎ አያውቅም፡፡ ሁሌ ዝም ነው። በአቅራቢያዋ ያሉ ሌሎች ተክሎች፣ ፅጌረዳዋን ለመምከር ቢሞክሩም እሷ ግን ከመጤፍ አልቆጠረቻቸውም። በውበቷ እጅጉን ትመካ ነበር።
በአንድ የሚያቃጥል የበጋ ወቅት ታዲያ በረሃው ድርቅ አለ። ለተክሎቹ ጠብታ ውሃ እንኳን አልነበረም። ፅጌረዳዋ ሃይለኛውን በጋ መቋቋም ተሳናት፤ መጠውለግም ጀመረች። የሚያምሩ የአበባ ቅጠሎቿ ደረቁ።
በዚህ መሃል ድንገት ወደ ቁልቋሉ ስታማትር፣ አንዲት ድንቢጥ ውሃ ለመጠጣት መንቁሯን ቁልቋሉ ላይ ሰክታ ተመለከተች። ለአፍታ ድንቢጧን መሆኗን አማራት፡፡ በመጨረሻ ግን በሃፍረት ተሸማቅቃ ቁልቋሉ ጥቂት ውሃ እንዲያጠጣት  ጠየቀችው። ደጉ ቁልቋልም ከመቅፅበት ተስማማ፡፡ በዚያ አደገኛ የበጋ ሙቀት ሁለቱንም (ድንቢጧንና ፅጌረዳዋን) በውሃ ጥም ከመሞት አተረፋቸው፡፡ ጉርብትና ማለት ይኼ ነው፡፡

Read 1409 times