Saturday, 04 June 2022 14:51

“ድቡሻ" የኪነ ጥበብ ምሽት በወላይታ ሶዶ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)


                “ድቡሻ” የተሰኘና በዓይነቱ ልዩ የሆነ የኪነጥበብ ምሽት በዛሬው ዕለት ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በወላይታ ሶዶ ከተማ በያዕቆብ ኢንተርናሽናል ሆቴል ይካሄዳል፡፡ በዚህ የኪነ ጥበብ ምሽት ግጥም፣ ዲስኩር፣ ግጥም በውዝዋዜ፣ ጌሬርሳ ሙዚቃ በጉንጉን ባህላዊ ባንድና ሌሎች ዝግጅቶች እንደሚቀርቡም ታውቋል፡፡
 በምሽቱ ገጣሚ ኤሊያስ ሽታሁን፣ ገጣሚ ተስፋሁን ከበደ (ፍራሽ አዳሽ)፣ ገጣሚና ተወዛዋዥ ኤፍሬም መኮንን (ኤፊ ማክ) እና ሌሎችም የሶዶ ከተማ ወጣት ገጣሚያን የግጥም ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ተስፋሁን ከበደና ኤፍሬም መኮንን በጥምረት የሚታወቁበትን ግጥም በውዝዋዜ ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
የኪነ ጥበብ ምሽቶችን በማዘጋጀት የሚታወቁት አንጋፋዎቹ ጋዜጠኞች ምስክር ጌታነው በፕሮግራሙ ተገኝቶ ልምዱን እንደሚያካፍል የተነገረ ሲሆን ከጎንደር ከአዲስ አበባና ከሀዋሳ የጥበብ ምሽቱን ለመታደም በርካታ እንግዶች እንደሚሄዱም ታውቋል፡፡
“ድቡሻ” ማለት በዳውሮ፣ በጋሞና በወላይታ አካባቢ ዛፍ ስር ተሰብስበው የሚመካከሩበት፣ ዕርቅ የሚያወርዱበትና አንድነት የሚገለጽበት ባህል መሆኑን የፕሮግራሙ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ትዕግስት ታንቱ አብራርታለች፡፡

Read 11270 times