Thursday, 02 June 2022 16:08

ኢትዮ ቴሌኮም በ66 የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የዲጂታል መማሪያ ማዕከላትን አቋቋመ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ ብሎም የነገ ሃገር ተረካቢ ዜጎችን በዕውቀት ለማነጽ የሚደረገውን ሁለገብ ሀገራዊ ጥረት ለማገዝ፣ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች በተመረጡ 66 የመንግሥት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ኮምፒውተሮች፣ ልዩ ልዩ የትምህርት ቤት መገልገያ መሳሪያዎችንና ከፍተኛ ፍጥነት ያለው መደበኛ የብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት በማሟላት ያቋቋማቸውን የዲጂታል መማሪያ ማዕከላት (digital learning centers) በዛሬው እለት አስመርቋል፡፡
ኩባንያው በመላ አገሪቱ ለሚገኙ 66 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ45.48 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ 1 ,386 ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮችን፣ 1,386 ጠረጴዛዎችና ወንበሮችን፣ የትምህርት ቤት መገልገያ መሳሪያዎችን በማሟላት የዲጂታል የመማሪያ ማዕከሎቹን ያቋቋመ ሲሆን በዚህም ከ140, 596 በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
ከእነዚህ 66 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 18 ትምህርት ቤቶች በአዲስ አበባ፣ ቀሪዎቹ 48 ትምህርት ቤቶች ደግሞ በክልሎች የሚገኙ ሲሆን የተጠቃሚ ትምህርት ቤቶቹ የተመረጡት በአዲስ አበባና ክልል ትምህርት ቢሮዎች ከኢትዮ ቴሌኮም የሪጅንና የዞን ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር መሆኑ ታውቋል፡፡

Read 4086 times