ኡጉር የተባለችዋ የቻይና ግዛት በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎችን እያፈሰች በገፍ ወደ እስር ቤት በማጋዝ በመላው አለም አቻ እንደማይገኝላት በመረጃ መረጋገጡንና ከግዛቷ 25 ነዋሪዎች አንዱ በሽብርተኝነት ተከስሶ በእስር ቤት እንደሚገኝ ዘ ጋርዲያን ከሰሞኑ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
አሶሼትድ ፕሬስ አገኘሁት ያለውን መረጃ መሰረት አድርጎ በዘገባው እንዳለው፣ ኡጉር በተባለችውና ሙስሊሞች በሚበዙባት የቻይና ግዛት ህጻናትና አረጋውያንን ጨምሮ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች በሽብር ተከስሰው በእስር ላይ እንደሚገኙና ከ2 እስከ 25 አመት በሚደርስ እስር እንደተቀጡ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡መረጃው የቻይና መንግስት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን በተለያዩ ሰበቦች በእስር ቤት አጉሮ ይገኛል የሚለውን ውንጀላ የሚያጠናክር ነው መባሉን የጠቆመው ዘገባው፤ መንግስት በተለይ አናሳ ሙስሊሞች በሚበዙባት ኡጉሩ እየፈጸመው የሚገኘውን የጅምላ እስርም የሚያረጋግጥ ነው ብሏል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል