Saturday, 21 May 2022 12:51

የተጠላው እንዳልተጠላ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ምዕራፍ ስምንት

          ጥርሱ ያለቀው አዛውንት
ፊቱን መምህሩ ፊት ላይ ደቅኖ እንዲህ አለ፡-
#ወንጀለኛውና ትንሹ ሰይጣን፤
ባንዲራችን ከንቱ፤
ሀገራችን ባዶ፤
ዜግነታችን ቆሻሻ፤
ድንበራችን ገሃነም፤
ሉአላዊነታችን ስድብ እንደሆነ አልክ፡፡
እንደምን ድንቅ ተናግረሃል፤
ግንኮ ኢትዮጵያ ለኛ ደግ እንደሆነች ሁሉ
ላንተም ቸር ነበረች፡፡
ስለምን ከዳሀት?;
መምህሩ ሲደበደብ የላላ ደበሎውን አጠባብቆ በትንሽ ፋታ ህመሙን ካስታገሰ
በኋላ እንዲህ አለ---
#ሐገራችሁ ደግ ነበረች፤
ቸርም ነበረች፡፡ ለናንተ ግን አይደለችም፡፡
በስንፍናችሁ ያስጨከናችኋትም እናንተ ናችሁ፡፡ኢትዮጵያ ወድቃ፣ በስብሳና አጎንቁላ የምታፈራ ፍሬ ሳትሆን በጎተራ የምትሞሸር
የደደረች ዘር ሆናለች፡፡
ኢትዮጵያውያን፤
ሬሳ እንዳይፈርስ አዘውትረው የሚታትሩትን የጥንት ግብጻውያንን ይመስላሉ፡፡
እናንት ከእመቤት ኢትዮጵያ አስክሬን ጋር ከነህይወታችሁ የተቀበራችሁ ባሮች፤
የሞተን እንቅልፍ ለማስወገድ ያዘጋጃችሁትን ዝማሬ አታውርዱ፤
እናንተ የሙት ሞግዚቶች
ኢትዮጵያ የሚለው መወድሳችሁ ያብቃ!
ኢትዮጵያ በረዥም ዕረፍት ውስጥ ያለ ጣዕር ሞታለች፡፡ መወድሳችሁን
አቁማችሁ ለፍታት መቋሚያችሁን አንሱ!
መቃብር ቆፋሪውን ቀስቅሱና እያፏጨ ይቅበራት፡፡
የታማሚ ሞት የአስታማሚ ነጻነት እንደሆነ አታውቁምን?
እናንተ አስክሬን አስታማሚዎች፤ እናንተን በመጠበቅ የቀብር መልስ ንፍሯችሁ
ነፍስ ዘራ፤
ጉዝጓዛችሁን መሬት ዋጠው--;
#ኡ! ኡ! ኡ!;
#ሁሉን ዘረፈን!;
#አድባር መስሎ የለም እንዴ?;  አለ አንድ ሰላላ ድምጽ
#መቼም ከድንጋይ ሳይሻል አይቀርምና
አንገቱን ቆርጣችሁ ጭንቅላቱን ትከሉልን
ቅቤ እንቀባው--;
#ኢትዮጵያውያን; ሲል በአካባቢው ያለ ድምጽ እረጭ አለ
#ሀገር ይዘው ህዝብ ይፈልጋሉ፡፡ እንደ እስራኤሎች ህዝብ ይዘው ሀገር በፈለጉ እንዴት ደግ ነበር፤እንደ አሜሪካኖች መስፈሪያ ያጣች የሰፋሪዎች ጀልባ ብንሆን እንዴት መልካም ነበር;
(ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ #የተጠላው እንዳልተጠላ; አዲስ መጽሐፍ የተቀነጨበ)

Read 11094 times