Saturday, 02 April 2022 11:26

“ኢትዮጵያ ሪድስ” አዲስ የህፃናት ቤተ መፃሀፍት አስመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

       “ኢትዮጵያ ሪድስ” የተሰኘውና በልጆች ንባብ  ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራው ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት በጎተራ የጋራ መኖሪያ መንደር ውስጥ ዘመናዊ የህፃናት ቤተ መፃሀፍት አስመረቀ፡፡ ግብረ ሰናይ ድርጅቱ ቤተ መፃሀፍቱን የህፃናት አዕምሮ በሚገነቡ በርካታ መፃፍትና ቁሳቁሶች አሟልቶ ያስመረቀው ባለፈው ቅዳሜ መጋቢት 17 ቀን 2014 ዓ.ም ረፋድ ላይ ነው በምረቃ ሥነ ስርአቱ ላይ የኢትዮጵያ ሪድስ የአገር ውስጥ ተጠሪ ወይዘሪት የምስራች ወርቁ የጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች፣ህፃናት የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በምረቃው ስነ ስርዓቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶችና የህፃናት መፃህፍት ደራሲያን ለህፃናት ተረት ያነበቡ ሲሆን ህፃናትም ህብረ ዝማሬን ለታዳሚ አቅርበዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሪድስ ባለፉት 20 ዓመታት የህፃናት ንባብ ላይ ትኩረቱን አድርጎ ቤተ መፃፍትን በከተማና በገጠር በመገንባት በርካታ ቋንቋዎች የህፃናት መፅህፍትን በማሳተምና በመለገስ እየሰራ ይገኛል፡፡

Read 20180 times