Thursday, 13 January 2022 06:22

ፕሬዚዳንቷ የተገደሉባት ሃይቲ ጠ/ሚኒስትር ከግድያ አመለጡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ፕሬዚዳንቷ ዩቬኔል ሞይሴ ከወራት በፊት በታጣቂዎች ጥቃት በተገደሉባት ሃይቲ፣ ባለፈው ቅዳሜ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ኤርየል ሄንሪ ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው ለጥቂት ማምለጣቸው ተሰምቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዕለቱ ጎናቪስ በተባለችው የአገሪቱ ከተማ የአገሪቱን የነጻነት በዓል ለማክበር በተከናወነ ስነስርዓት ላይ በታደሙበት አጋጣሚ በታጣቂዎችና በፖሊስ መካከል ግጭት መቀስቀሱንና ተኩስ እንደተከፈተባቸው የዘገበው አልጀዚራ፣ ፕሮግራሙን አቋርጠው እንዲሄዱ ከተደረገ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ #አገራችንን ለገንዘብ ሲሉ ቀውስ ውስጥ ለመዝፈቅ ለሚታትሩ ሃይሎች እጅ አንሰጥም; ሲሉ መናገራቸውንም አመልክቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርየል ሄንሪ የቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዩቬኔል ሞይሴ ባለፈው ሃምሌ ወር በቤተመንግስታቸው እያሉ በታጣቂዎች በተፈጸመባቸው ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ፣ አገሪቱን የማስተዳደር ስልጣኑን ይዘው እንደሚገኙ ያስታወሰው ዘገባው፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ በተከፈተው ተኩስ አንድ ሰው መሞቱንና ሁለት ሰዎች መቁሰላቸው መነገሩንም አስረድቷል፡፡

Read 4849 times