Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 15 September 2012 13:32

አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ከሞት ተረፉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ሰኞ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ሀሰን ሼክ መሀመድ ረቡዕ እለት ከተሞከረባቸው ግድያ አመለጡ፡፡ ለግድያ ሙከራው አልሸባብ ሀላፊነቱን ወስዷል፡፡ ፕሬዚዳንቱ የኬኒያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርን ተቀብለው እያነጋገሩ ባሉበት ወቅት ከሆቴሉ ውጪ የቦምብ ፍንዳታ ድምጽ መሰማቱን የገለፀ በቦታው የነበረ አንድ የፖሊስ መኮንን፤ በጥቃቱ አንድ ዩጋንዳዊ የሠላም አስከባሪና ሁለት የሶማሊያ ወታደሮች እንደሞቱ ሦስት ወታደሮች ደግሞ እንደቆሰሉ ተገልጿል፡፡ ጥቃቱን ከፈፀሙት የአልሸባብ አጥፍቶ ጠፊ ሶስት ወታደሮች ውስጥ አንደኛው በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ማለፉ ታውቋል፡፡

የአልሸባብ ቃል አቀባይ አሊ መሐመድ ለኤፍፒ በሰጡት መግለጫ፤ በፕሬዚዳንት ተብዬው እና በኬኒያው የውጪ ጉዳይ ሚ/ር ላይ ለተሞከረው ግድያ ሀላፊነቱን እንወስዳለን” ያሉ ሲሆን “የምርጫ ሂደቱ ህጋዊ አይደለም፡፡ ከተመራጩ ፕሬዚዳንት ጋር ምንም አይነት የግል ቁርሾ የለንም፡፡ ነገር ግን ሂደቱ በሙሉ የጠላት ፕሮጀክት ነው” ብለዋል፡፡

ጥቃቱን ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት የውጪ ፖሊሲ ሃላፊ ካትሪን አሽተን፤ የግድያ ሙከራው የተፈፀመው በፕሬዚዳንቱ እና በቅርቡ እየታየ ባለው የሶሚሊያ የፖለቲካ መረጋጋት ላይ ነው በማለት የግድያ ሙከራውን አውግዘዋል፡፡ “የሰኞው ሰላማዊውና ውጤታማው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የተስፋ እና የለውጥ ጭላንጭልን ያሳየ ነበር” ብለዋል፤ካተሪን አሽተን፡፡

 

 

Read 3785 times Last modified on Saturday, 15 September 2012 13:41