Sunday, 14 November 2021 00:00

የአካል ጉዳተኛ ህጻናት ቁጥር ከ240 ሚ. ማለፉ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በመላው አለም የአካል ጉዳተኛ ህጻናት ቁጥር ከ240 ሚሊዮን ማለፉንና ህጻናቱ የመብቶቻቸው ተጠቃሚዎች እንዳይሆኑ የሚያግዷቸው እንቅፋቶችና ፈተናዎች እየተበራከቱ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ሰሞኑን ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ የህጻናትን አጠቃላይ ደህንነት ሁኔታ ለመገምገም የሚያስችሉ 60 ያህል ነጥቦችን መሰረት በማድረግ በ42 የአለማችን አገራት የሰራውን ጥናት ውጤት ባካተተበት ሪፖርቱ እንዳለው፣ የአካል ጉዳተኛ ህጻናት በአብዛኛው ከሌሎች ህጻናት ጋር ሲነጻጸር ተገቢው ትኩረት አይሰጣቸውም፡፡
አካል ጉዳተኛ ህጻናት በማህበረሰባቸው ውስጥ በበቂ መጠን ተሳትፎ እንዳያደርጉ ጫና እንዳለባቸውና የተመጣጠነ ምግብና የንጹህ ውሃ አቅርቦት በበቂ መጠን እንደማያገኙ የጠቆመው ሪፖርቱ፣ ለተለያዩ አካላዊና ልቦናዊ ጥቃቶች እንዲሁም ለጉልበት ብዝበዛ እንደሚዳረጉም አመልክቷል፡፡
የአካል ጉዳተኝነት ችግር ያለባቸው ህጻናት ከሌለባቸው ጋር ሲነጻጸር፣ ከትምህርት ገበታ ውጭ የመሆን፣ አነስተኛ የንባብ ችሎታ የመያዝ፣ ደስተኛ ያለመሆን እድላቸው ከፍ ያለ እንደሆነም ሪፖርቱ አብራርቷል፡፡


Read 2695 times