Saturday, 23 October 2021 12:43

የአዕምሮ ጤና የኪነ ጥበብ፣ፌስቲቫል ኤግዚቢሽንና ጉባኤ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ዳጉ ኮሙኒኬሽን ከቅዱስ አማኑኤል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ከጥቅምት 18 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀንን በኪነጥበብ ፌስቲቫል በኤግዚቢሽንና የአዕምሮ ጤና ላይ ባተኮረ ጉባኤ ሲያከብር ነው።
 በዚህ ፌስቲቫል አዕምሮ ጤና ላይ የሚያተኩሩና ለማህበረሰቡ ግንዛቤን የሚፈጥሩ የኪነጥበብ ሥራዎች፣ በአዕምሮ ጤና ላይ የሚሰሩ ማዕከላትና ድርጅቶች የሚሰሯቸውን ስራዎችና የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ለጎብኚ የሚያሳዩበት ኤግዚቢሽንና የአዕምሮ ጤና ላይ ትኩረት ያደረጉ ጉባኤዎች እንደሚካሄዱበት የዳጉ ኮሙኒኬሽን ባለቤትና ዋና ስራ አስኪጅ ጋዜጠኛ ማናዬ እውነቱ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል።
በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን ከጥቅምት 18 ጀምሮ በኢትጵያ ብሄራዊ ቴአትር እንደሚቀርቡም ጋዜጠኛ ማናዬ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

Read 12874 times