Monday, 04 October 2021 00:00

ኳታር ኤርዌይስ ገቢው በ4 ቢሊዮን ዶላር ቢቀንስም የአለማችን ቁጥር አንድ ተብሏል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ኳታር ኤርዌይስ ባለፈው የፈረንጆች አመት ከኮሮና ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ አመታዊ ገቢው በ4 ቢሊዮን ዶላር እንደቀነሰ ባለፈው ሰኞ ቢያስታውቅም፣ በአመቱ የአለማችን ቁጥር አንድ አየር መንገድ መባሉን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
ስካይትራክስ የተባለው ተቋም ከሰሞኑ ይፋ ያደረገውን የአመቱ የአለማችን ምርጥ አየር መንገዶች ዝርዝር ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣  አየር መንገዱ ለ6ኛ ተከታታይ አመት ነው የአመቱ ምርጥ ተብሎ ለመመረጥ የበቃው፡፡ ሲንጋፖር ኤርላይንስ፣ ኤኤንኤ ኦል ኒፖን ኤርዌይስ፣ ኤሜሬትስ፣ ጃፓን ኤርላይንስ፣ ካቲ ፓሲፊክ፣ ኢቫ ኤር፣ ኳንታስ ኤርዌይስ፣ ሃኒያን ኤርላይንስና ኤር ፍራንስ በአመቱ የስካይትራክስ የአለማችን ምርጥ አየር መንገዶች ዝርዝር ውስጥ ከሁለተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

Read 2639 times