የአለማችን 2ኛው ግዙፍ የሞባይል አምራች ኩባንያ የሆነው የአሜሪካው አፕል ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ለገበያ ያቀረባቸው የአይፎን ስማርት ስልኮች ቁጥር ከ2 ቢሊዮን ማለፉን አንድ ዘገባ አመልክቷል፡፡
በመላው አለም ስማርት ስልኮችን ከሚጠቀሙ 3.8 ቢሊዮን ያህል ሰዎች መካከል 26 በመቶ ያህሉ የአይፎን ተጠቃሚዎች መሆናቸውን የዘገበው ዳብሊውሲሲኤፍቴክ የተባለ ድረገጽ፣ በአሜሪካ 60 በመቶ ያህል የስማርት ስልኮች ተጠቃሚዎች አይፎን እንደሚጠቀሙም አመልክቷል፡፡
አፕል በተለይ በቅርቡ ያወጣው አዲሱ ምርቱ አይፎን 13፤ ከዚህ ቀደም ያልነበሩ በርካታ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ያካተተ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሽያጩ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተነግሯል፡፡