Saturday, 25 September 2021 00:00

የእውቁ የናዊ ከፍፌ ኦልይድ ኮንሰርት ተካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የእውቁ አፍሪካዊ አርቲስት ኮፍፊ አሊይድ ኮንሰርት ትላንት በክለብ አዲስ ተካሄደ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኮፍፊ ኦሊድ በተሰኘ የመድረክ ስሙ የሚታወቀው ተወዳጁ አርቲስት አንቶን ክሪስቶፍ አጌፓ ሙምባ ኦሎሚዴ ትላንት በክለብ አዲስ ስራዎቹን አቅርቧል፡፡
በክለብ አዲስ አዘጃጅነት በተካሄደው በዚህ ኮንሰርት ላይ አንጋፋው አርቲስት ስራዎቹን በማቅረብ ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በአንድ ላይ አገናኝቶ ያዝናና ሲሆን፣ ዘ ክለብ አዲስ “የ2021 የአፍሪካ ህብረት የሆነውን በስነ-ጥበብ፣ባህልና ቅርስ ሀብቶቻችንን በመጠቀም የምንፈልጋትን አፍሪካ መገንባት” የተሰኘውን መሪ ቃል ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የአፍሪካዊያን ውብ ሀብቶቻችንን የሚያሳዩ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን ማቅረቡም አስታውቋል፡፡
አንጋፋው አፍሪካዊ አርቲስት ከፍፊ ሶኩስ ዘፋኝ፣ ዳንሰኛ፣ፕሮዲዩሰርና አቀናባሪ ሲሆን በስራው በርካታ ወርቃማ ሽልማቶችን ከማግኘቱም በላይ ከነአ ፊሊ ኡፑፓ እና ፌሪ ጎ ከመሳሰሉ ዝነኛ አፍሪካዊያን አርቲስቶች ጋር በመሆን ታዋቂውን “ሩብ ላቲን ኢንተርናሽናል” ኦርኬስትራን መስርቷል፡፡ ይህን አንጋፋና ተወዳጅ አርቲስት ነው ዘክለብ አዲስ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አዲስ አበባ በማስመጣት ኮንሰርት እንዲያቀርቡ ያደረገው፡፡
በኮንሰርቱ ላይ አፍሪካን ሙዚቃና ጥበብ አፍቃሪያ፣የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች ተወካዮች፣አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች የኮንጎ ማህበረሰብ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች መታደማቸውም ታውቋል፡፡


Read 23963 times