Monday, 27 September 2021 13:04

የማህጸን ፍሬ ካንሰር፡፡

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    በአለም አቀፍ ደረጃ ያለው የካንሰር ሁኔታ እ.ኤ.አ በ2020 ሲገመት 19.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በአዲስ በካንሰር ሕመም ይያዛሉ፡፡ ወደ 10.0 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ በሕመሙ ምክንያት ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡ የአለም የጤና ድርጅት የካንሰር ምርምር እንዳረጋገጠው ደግሞ የማህጸን ካንሰር በአለም ላይ በሴቶች ላይ በ8ኛ ደረጃ የሚከሰት ሕመም ሲሆን ከሌሎች ካንሰር ሕመሞችም የ18ኛ ደረጃ የሚሰጠው አስከፊ ሕመም ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2018 በተደረገው ጥናት የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በአለም ላይ በአመቱ ወደ 300‚000 የሚደርሱ በህመሙ በአዲስ የሚያዙ ሴቶች ለህክምና ቀርበዋል፡፡  
በአለም ላይ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ህመሞች መኖራቸው ሲታወቅ መፍትሔ የሚገኝላቸው ቢሆንም የካንሰር ሕመም ግን በአብዛኛው ሕመሙ ሲከሰት ጀምሮ ምልክት ላያሳይ ስለሚችል ሰዎችን ለህልፈት ይዳርጋል፡፡ ከጅምሩ ምንም ምልክት ከማያሳዩት የካንሰር ሕመሞች መካከል የማህጸን ካንሰር አንዱ ነው፡፡ ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ማእከል መምህርና ረዳት ፕሮፌሰር በአንድ ወቅት የሰጡትን ማብራሪያ ከወቅታዊ መረጃዎች ጋር አዛምደን እናስነብባችሁ፡፡
በዚህ እትም የምናስነብባችሁ የማህጸን ፍሬ ካንሰር ስለሚባለው ሕመም ነው፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በማህጸን ፍሬ ላይ የሚወጡ እጢዎች በግምት ከ30-50 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ሊኖራቸው ይችላል፡፡ የማህጸን ፍሬው እጢ በቀዶ ሕክምና ከተወገደ በሁዋላ ሕክምናው በዚያ አያበቃም፡፡ የካንሰር ሴሉ ወደአካባቢው ተሰራጭቶአል ወይንስ አልተሰራጨም የሚለው የሚለየው በቀጣይ በሚደረጉ ሕክምናዎች ነው፡፡ አንዲት ሴት በማህጸን እጢ ላይ የካ ንሰር ሕመም ቢገጥማት መዳን ያለመዳንዋ የሚለየው ባላት እድሜና የካንሰር ሕመሙ ባለው ደረጃ መሰረት ነው፡፡ እንደሚታወቀው የካንሰር ሕመም አራት ደረጃ ያለው ሲሆን በአንደኛ ደረጃ ያለው ካንሰር ሕክምና ካገኘ ቶሎ የሚድን ሲሆን በሁለተኛነት ደረጃም ያለው እንዲሁ ጥብቅ ክትትልና ሕክምናን ይፈልጋል እንጂ በአስተማማኝ ሊድን ይችላል የሚል የባለሙያዎች ምስክርነት አለው። በሶስተኛነት ደረጃ የሚገኘው የካንሰር ሕክምና ጠበቅ ያለና ጊዜ የሚፈጅ ሕክምና የሚፈልግ ሲሆን ለመዳን አስተማማኝ ተስፋ የማሰጥበት ነው። በአራተኛ ደረጃ የሚገኘው እጅግ አስቸጋሪው የካንሰር ሕመም ደረጃ ነው እንደባለሙያዎቹ ትንታኔ፡፡
የማህጸን ፍሬ ማለት ልክ እንደወንድ ልጅ የዘር ፍሬ መያዣ እንደሚባለው ሲሆን የወንድ ልጅ አካል ወደ ውጭ ወጥቶ ይታያል፡፡ የሴት ልጅ ግን በሆድ እቃ ውስጥ ከማህጸን ጋር ተያይዞ የሚገኝ ነው፡፡ የማህጸን ፍሬው ወይንም እንቁላሉ በግራና በቀኝ በኩል የሚገኙ ሲሆን ይህ አካል የሴት ልጅን ሴት የሚያሰኝ ባህርይ የሚሰጥ ነው፡፡ የማህጸን ፍሬዎች ሴትን ሴት ለማ ለት የሚያስችሉ ባህርያትን የሚፈጥር ሲሆን እነሱም እንደ ጡት፤የሰውነት ቅርጽን የመሳ ሰሉን እና በመቀመጫ አካባቢ ያለውን ውፍረት የመሳሰሉት ከእንቁላሉ ስራ ጋር የሚያያዙ ባህርያት ናቸው፡፡ የማህጸን ፍሬ ከዚህም ባለፈ ሴቶች በየወሩ የወር አበባ እንዲኖራቸው እና ማህጸን በትክክል ተፈጥሮአዊ ሂደቱን እንዲያከናውን የሚያደርጉ አካላት ናቸው፡፡
የማህጸን ፍሬ ያለበትን ማእቀፍ ልክ እንደከረጢት ያለ ሲሆን እንቁላሎቹ በከረጢቱ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ከከረጢቱ፤ ከእንቁላሎቹ እንዲሁም በመካከል ካለው ቱቦ የሚነሳ እጢ ወይንም ካንሰር ሊኖር ይችላል፡፡ በሁሉም ቦታዎች የሚገኙ እጢዎች ሲከሰቱ ገና ከጅምራቸው ምልክት ላይ ሰጡ እና ሳይታወቅ ጉዳት ሊያደርሱ ይችላሉ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ጉዳት የሚያደርሰው ከእንቁ ላል ከረጢቱ ላይ የሚነሳው ነው፡፡ ይህ የእንቁላል ከረጢት ካንሰር ይበልጥ ገዳይ ነው፡፡ የማህጸን ፍሬ ወይም የእንቁላል ከረጢት ላይ የሚነሳው ካንሰር በባህርይው ወደሌላ የሰውነት ክፍል የማይዛመት ሲሆን በዚያው አካባቢ እያደገ ሆድን ሊያሳብጥ፤ሽንትና ሰገራን መከልከል የመሳሰሉትን ሕመሞች ያስከትላል፡፡ ይህ የካንሰር ሕመም ምንም እንኩዋን ገዳይና አስከፊ ነው ቢባልም በጊዜው ከታከመ ግን ሊድን የሚችል መሆኑ እሙን ነው። ከዚህም ውጭ የማህጸን ፍሬዎች በካንሰር የመታመም ሁኔታ አልፎ አልፎ አንዱ ቢጠቃ አንዱ ሊተርፍ ስለሚችል ወደሌላ ደረጃ ከመድረሱ በፊት ሕክምና ከተደረገለት ተፈጥሮአዊ ሂደቱን በአንዱ መቀጠል ይችላል፡፡ ለምሳሌም ሁለት ሁለት እየሆኑ እንደተፈጠሩት እንደ እጅ ፤እግር ፤አይን እና ኩላሊት እነዚህም ፍሬዎች ሁለት ስለሆኑ አንዱ ቢጎዳ በአንደኛው መኖር ይቻላል፡፡ ነገር ግን ጉዳቱ ኃያል ሆኖ ለሞት እንዳያደርስ አስቀድሞ ምርመራ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡
አንዲት ሴት የማህጸን ፍሬ ካንሰር እንደሚይዛት አስቀድማ የምታውቅበት ምንም ምልክት ላታይ ትችላለች፡፡ የካንሰር ሕመሙ ሲጀምር ለጥርጣሬ የሚበቃ የህመም ስሜት ስለሌለው ብዙዎች የሚያውቁት ሕመሙ ከጠና በሁዋላ ነው፡፡ በገዳይነቱ ከፍ ያለ ደረጃ የሚሰጠውም በዚህ ምክንያት ነው፡፡ የማህጸን የካንሰር ሕመም ለመከላከል ወይም አስቀድሞ ጥንቃቄ ለማ ድረግ አስቸጋሪ በመሆኑም የሚመከረው ቅድመ ምርመራ ማድረግ ነው፡፡ የማህጸን ፍሬ ካንሰር ሕክምና እንደታማሚዎቹ እድሜና የካንሰር አይነት ይወሰናል፡፡ ብዙ ጊዜ እንደሚታየው በእድ ሜያቸው እስከሀያ አመትና በዚያ አካባቢ ያሉት ሴቶች የሚያዙት ከእንቁላሉ በሚነሳው ካንሰር ነው፡፡  
የማህጸን ፍሬ ካንሰር ልጅ በመውለድ እድሜ ላይ ያሉ ሴቶችን  ጭምር የሚይዝ በመሆኑ ህክምናው ከተደረገ በሁዋላ ልጅ የመውለድ እድሉ ሊኖርም ላይኖርም እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ሕመሙ የተከሰተው በአንደኛው የማህጸን ፍሬ ላይ ከሆነ እና አንዱ ግን ከህመሙ ንጹህ ከሆነ የታመመው አካል በቀዶ ህክምና ተወግዶ በጤነኛው ፍሬ አማካኝነት ልጅ መው ለድ ይቻላል፡፡ ሁለቱም የማህጸን ፍሬዎች ከታመሙ እና በኦፕራሲዮን የሚወገዱ ከሆነ ግን ልጅ መውለድ አይታሰብም፡፡ የህክምናው ዘርፍ ምንጊዜም በቅድሚያ የሚያስበው ሴትየዋን ማዳን እንጂ ልጅ ስለመውለድ አይደለም፡፡ በእድሜአቸው ልጅ ከመውለድ የዘለሉ ሴቶች ግን ሁለ ቱም ይሁን አንዱ የዘር ፍሬአቸው በካንሰር ቢታመም ስለ ልጅ መውለድ መጨነቅ ሳይኖ ርባቸው በቀጥታ እንደህመሙ ሁኔታ ሕክምናውን ያገኛሉ፡፡ አንዲት ሴት እድሜዋ በወጣ ትነት ክልል ውስጥ እያለ በዚህ የካንሰር ሕመም ብትታመም እና ሁለቱም የዘር ፍሬዎቿ ወይንም ማህጸ ንዋ በቀዶ ህክምና እንዲወገድ የሚያሰገድድ ሁኔታ ቢያጋጥም ይህች ሴት በወ ደፊት ሕይወትዋ በሴትነትዋ ልታገኘው የሚገባትን ብዙ ነገሮች ሊያሳጣት ስለሚችል ከባድ ነው፡፡ ስለዚህ ማንኛዋም ሴት ለዚህ ሕመም ሳትዳረግ በተወሰነ የጊዜ እርቀት ወደ ሐኪም እየቀረበች ስለመራቢያ አካላት የካንሰር ሕመም ሁኔታዋ ከሕክምና ባለሙያ ጋር መመካከር ይጠቅማታል፡፡ ሕክምናው ከተጀመረ በሁዋላም ብዙዎች በራሳቸው ውሳኔ ስለዳንኩኝ ሕክም ናው ይበቃኛል በማለት የህክምና ክትትላቸውን ማቋረጥና መድሀኒታቸውንም በትክክል ከመ ውሰድ የሚታቀቡበት ሁኔታ ስላለ ባልታሰበ ሁኔታ የካንሰር ሴሉ ለመሞት ከሚያበቃቸው ደረጃ ሊያደርሳቸው ይችላል፡፡
አንዲት ሴት በካንሰር ሕመሙ ትያዝ አትያዝ ለማወቅ አይቻልም ቢባልም ህመሙ ደረጃው ከፍ ሲል ግን አንዳንድ ስሜት መኖሩ አይቀርም። ሕመሙ የሚሰማቸው ግን የካንሰር ደረጃው ከፍ እያለ ሲሄድ ነው፡፡ የካንሰር ሕመም ከአንድ እስከ አራት ደረጃ ያለው ሲሆን ህመሙ መሰማት የሚጀመረው ከሁለተኛ ደረጃ ጀምሮ ነው፡፡ የካንሰር ሕመሙ ደረጃውን ሲጨ ምር ሕክምናውንም ውስብስብ ሊያረገው ይችላል። የካንሰር ሕመሙ በአንደኛ ደረጃ ሲሆን ለህ ክምና ቢቀርቡ እስከ 80% የሚሆኑት ታካሚዎች ሙሉ በሙሉ ማዳን ይቻላል፡፡ የካንሰር ሕመሙ መኖሩ የሚሰማው ከእንቁላሉ ከረጢት ወጥቶ የማህጸን አካባቢን ነካክቶ ወደ ሆድ እቃ ውስጥ ሲገባ እና የተለያዩ ሕመሞችን ማሰማት ሲጀምር ነው። ለምሳሌም ምግብን ሲመገቡ ቶሎ መጥገብ፤ የምግብ አለመስማማት፤ የጨጉዋራ ሕመም፤ ቶሎ መጥገብ የመሳሰሉት እና ሰገራና ሽንት ላይ ችግር ማስከተል ሲኖር ነው፡፡ ስለዚህ ማንኛዋም ሴት በሆድዋ አካባቢ ሕመም ሲሰ ማት ለህክምና መሄድ ያለባት ወደ ውስጥ ደዌ ሕክምና ብቻ ሳይሆን ወደ ማህጸን ህክምናም ጭምር መሆን አለበት፡፡
ከማህጸን ፍሬ የሚነሳው ካንሰር ብዙ ጊዜ የሚያጠቃው ልጅ ያልወለዱ ሴቶችን ነው፡፡ ጡት ያላጠቡ እና የእርግዝና መከላከያ መድሀኒትን ያልወሰዱም ችግሩ ሊገጥማቸው እንደሚችል ይገ መታል፡፡ የእርግዝና መከላከያ እርግዝናን ከመከላከል ባሻገር የማህጸን ፍሬ ካንሰርንም ሊከላከል እንደሚችል የተረጋገጠ ነው፡፡ በቤተሰብ ደረጃም የማህጸን ካንሰር ሕመም ከነበረ በካንሰሩ የመ ያዝ እድል ይኖ ራል፡፡ ልጅ መውለድ በካንሰሩ ላለመያዝ እንደ ጥሩ አጋጣሚ ነው ሲባል ግን በእቅድና በፕላን መሆን እን ዳለበት ሳይዘነጋ መሆኑን ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡



Read 10331 times