Print this page
Sunday, 26 September 2021 00:00

ኢዜማ በጦርነት ለተፈናቀሉ ዜጎች ከ2 ሚ. ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)፤ በሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ባለው ጦርነት ምክንያት ከሃብት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች፣ የተለያዩ የቁስ ድጋፎችና እርዳታ እያደረገ መሆኑን  አስታውቋል።
ፓርቲው በስልጣን ላይ ካለው መንግስት ጋር ያለውን የፖለቲካ ልዩነት ወደ ጎን አድርጎ፣  በህወሃት ጥቃት የተፈጸመባቸውን ዜጎች የመታደግ ተግባር ላይ መጠመዱን ያመለከተ ሲሆን በጎንደር፣ ደሴና አፋር ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል። ከሰሞኑም የህወሃት ሃይል የከፋ ጭፍጨፋ በፈጸመበት በሰሜን ጎንደር ጭና ቀበሌ  በመገኘት በከፍተኛ አመራሮቹ በኩል፣ ከአራት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል ተብሏል።
በህውሃት ወራሪ ሃይል ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሴቶችና ህጻናት እንደመሆናቸው ፓርቲው የንጽህና መጠበቂያና አልባሳትን ነው ድጋፍ ያደረገው ብለዋል-የፓርቲው የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ቡድን ዋና ሃላፊ ማስተዋል አስራደ።
ኢዜማ ለወገኖቹ የሚያደርገው ድጋፍ በዚህ እንደማቆምና ቀጣይነት እንዳለውም ተናግሯል።
ኢዜማ ከሰሜን ጎንደር በተጨማሪ በደሴና በአፋር ክልል ለሚገኙ የጦርነቱ ተጎጂዎችም ወደ የአካባቢዎቹ ባሰማራቸው ልኡካን አማካኝነት ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል።
በደሴ ከተማ ለሚገኙ የጦርነቱ ተፈናቃዮች፣ ከ1 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ አልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን መስከረም 13 ቀን 2014 ዓ.ም ያስረከበ ሲሆን በተመሳሳይ  ለአፋር ክልል ተፈናቃዮች የ7 መቶ ሺህ ብር ድጋፍ አበርክቷል።


Read 12228 times
Administrator

Latest from Administrator