Saturday, 18 September 2021 17:38

አሜሪካ ለግብጽ ለመስጠት ያቀደችውን የ130 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ እርዳታ ሰረዘች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


              የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የባይደን አስተዳደር፣ የግብጽ መንግስት በዜጎቹ ላይ የሚፈጽማቸውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ለማስተካከል እርምጃ እስካልወሰደ ድረስ ሊሰጠው የታቀደው የ130 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ እርዳታ መሰረዙን አስታውቋል፡፡
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ባለፈው ማክሰኞ የሰጡትን መግለጫ ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ የአሜሪካ መንግስት የተቃዋሚ አክቲቪስቶች እስራትን ጨምሮ በግብጽ መንግስት እየተፈጸሙ ያሉት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በእጅጉ ስላሳሰቡት ለአገሪቱ ሊሰጥ ካቀደው 300 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 130 ሚሊዮን ዶላሩን በጊዜያዊነት ለመሰረዝ ወስኗል፡፡
የመብት ተሟጋቾች የአሜሪካ መንግስት በአመቱ ለግብጽ ሊሰጥ ያቀደውን ወታደራዊ እርዳታ ሙሉ ለሙሉ እንዲያስቀር ቢጠይቁም፣ የባይደን አስተዳደር ግን 130 ሚሊዮን ዶላሩን ብቻ ማስቀረቱንና የግብጽ መንግስት የሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር ውጤታማ ስራዎችን መስራቱን ካረጋገጠ ብቻ ገንዘቡን እንደሚሰጥ ማስታወቁንም  ዘገባው አመልክቷል፡፡
የአሜሪካ መንግስት ላለፉት አራት አመታት ለግብጽ በየአመቱ የ1.3 ቢሊዮን ዶላር ወታደራዊ እርዳታ ሲሰጥ መቆየቱንም ዘገባው አስታውሷል፡፡


Read 1601 times