ለኢትዮጵያ ወሳኟን ጎል በዚምባቡዌ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ያስቆጠረው የዋልያዎቹ የመሃል ተከላካይ አስቻለው ታመነ ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት “በቅድሚያ መላውን የኢትዮጵያን ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለሁ። ይህ የአዲስ ዓመት ስጦታ ነው። ለረጅም ደቂቃ ጨዋታውን አቋርጠውት ነበር። ግብ ጠባቂውም የተለያየ ነገር ሲያደርግ ነበር ፤ ከባዕድ አምልኮ ጋር በተያያዘ። ሆኖም ፍፁም ቅጣት ምት በራስ የመተማመን ጉዳይ ነው። እኔም ያንን ብዙ ትኩረት አልሰጠሁትም። ከዚህ በፊት ፍፁም ቅጣት ምት ላይ ብዙ ችግር የለብኝም ፤ የእሱ ተግባርም ላይ ትኩረት አላደረኩኝም። በክለብም በብሔራዊ ቡድንም እመታ ስለነበር እና በእንደዚህ ዓይነት ነገር ስለማላምንበት የግብ ጠባቂው ተግባር አላደናገረኝም ፤ ምንም ውስጤን አልረበሸውም። በጥሩ ሁኔታም ላስቆጥር ችያለሁ።›› - ሶከር ኢትዮጵያ፡፡
Published in
ስፖርት አድማስ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል