Print this page
Saturday, 04 September 2021 17:42

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 "እኛም ከነሱ መማር አለብን ብለን ወስነን ነበር"
                             ሔኖክ ሔዳቶ


                 “TPLF 27 ዓመት ሲገዛ በትግራይ ሌላ ፓርቲ አልነበረም። እኛም ከነሱ መማር አለብን ብለን ወስነን ነበር፤ የምደብቅህ ነገር የለም”
ይህን የተናገረው የቀድሞው ኦዴፓ (እንዲሁም 360 አባላት ያሉት የብልጽግና ፓርቲ) ማዕከላዊ ምክር ቤት አባል ዶ/ር ሚልኬሳ  ነው፤ ከሀገር ከወጣ በኋላ ሰሞኑን OMN ላይ ቀርቦ ባደረገው ቃለምልልስ። ሚልኬሳ ይህን መልስ የሰጠው ጋዜጠኛው (ጉዮ ዋርዮ) በኦሮሚያ ስላለ እስርና ግድያ ምንጭ ምን እንደሆነ ለጠየቀው ጥያቄ ነው። አክሎም “የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት፣ ደጋፊዎች፣ እኛን የማይደግፉ በህብረተሰብ ተቀባይነት ያላቸው ሰዎች ሁሉ ጠላቶቻችን ናቸው ብለን አቅጣጫ አስቀመጥን። በዛ መሰረት የዞንና የወረዳው መዋቅር ማሰርና መግደል ውስጥ ገባ” ብሏል። በዚህም አላበቃም፤ “ለምንድነው የምታስሩት? አውጥታችሁ የምታደርጉትን አድርጉ ይባል ነበር ለበታች መዋቅሩ” ሲል ተናግሯል።
ዶ/ር ሚልኬሳ አንድ ሰሞን ዝነኛ የነበረው ATM (A-አዲሱ፣ T-ታዬ፣ M-ሚልኬሳ) የኦዴፓ ተተኪ ወጣቶች ጥምረት አንዱ ፊትአውራሪ ተደርጎ ይወሰድ የነበረ፣ ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲም በፌዴራሊዝም እና ህዝብ አስተዳደር ያስተምር የነበረ ሰው ነው። በዚህ ደረጃ ያሉ ሰዎች እንዴት ኦሮሚያን የሚያህል ሰፊና ብዝሃነት ያለው ክልል ብቸኛ ፓርቲ ለመሆን ቁጭ ብለው ተነጋግረው ሊወስኑ እንደሚችሉ ማሰቡ ይዘገንናል።
በአጭሩ፤ ኦሮሚያ ውስጥ ሊኖር የሚገባው አንድ ፓርቲ ብቻ ነው ብሎ ማመን ከተቻለ በኢትዮጵያ ደረጃም እንደዛ ለማመን የሚከለክል ነገር የለም። ብዙ ሰዎች ጭቆናን ሳይሆን ጨቋኙን እንደሚጠሉ፤ እድሉን ሲያገኙም ከተቃወሙት ጨቋኝ በላይ አፋኝ እንደሚሆኑ ነው በተደጋጋሚ እያየን ያለነው። በእርግጥ ሚልኬሳ ውስጥ ሆኖ በብዕር ሥም ይጽፍ እንደነበርና መረጃዎችን በማውጣት የተወሰነ ለውጥ ለማምጣት መሞከሩን ቢገልጽም፣ አብዛኞቹ ጥፋቶች ራሱ በተሳተፈበት መፈጸሙን አልካደም፤ ለማስተባበልም አልሞከረም።
ብቻ በጣም ያናድዳል!

Read 1699 times
Administrator

Latest from Administrator