Print this page
Saturday, 04 September 2021 17:38

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮጵያ ስታራምደው የነበረው ፌዴራሊዝም የሕብረ-ብሔራዊ (Multinational) ፌዴራሊዝምን መስፈርትን ያሟላ አይደለም!
                           ጌታሁን ሔራሞ



             መስከረም 24 መንግስት እንደሚመሠረት አፈጉባዔው አቶ ታገሰ ጫፎ ትናንት አስታውቀዋል፣ ከዚሁ ጋር ተያይዞ፦
አሁን ያለው ሕገመንግሥት...በተለይም ክልላዊው ኦቶኖሚው... ዜጎችን በሀገራቸው ነባርና መጤ በማለት ለሁለት የከፈለ መሆኑ ይታወቅ!
ሕገ መንግሥቱ በየክልሉ ያሉ አናሳ ብሔሮችን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን የማያከብር መሆኑ ይታወቅ...ሁሉም ብሔር ከክልሉ ውጪ አናሳ መሆኑ ይሰመር (የሐረሪ ብሔር በራሱ ክልልም ጭምር አናሳ መሆኑን ሳንዘነጋ)!
ስለዚህም ከሞላ ጎደል በሁሉም ክልሎች ወረቀት ላይ የተፃፈው የብሔር ብዝሃነት ፅንሰ ሐሳብ መሬት ላይ ወርዶ ተግባራዊ እንዲደረግ የ”Territorial Autonomy” መርህ መሻሻል እንዳለበት ከወዲሁ ይታወቅ። በሌላ አኳያ አንቀፅ 39 ለሁሉም ክልሎች በሕገ መንግሥት ደረጃ ክልላዊ ኦቶኖሚን መስጠቱ ይታወቅ ...The right for secession is meaningless without territorial autonomy! እናም አንቀፅ 39 ላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሰጥ ሁኔታዎች ይመቻቹ!
ከላይ የተዘረዘሩትን ሕገ መንግሥታዊ ግድፈቶችን ጠቅለል ስናደርጋቸው፦ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት በተለይም በክልሎች ደረጃ ሁሌም የሚለፈፍለትን የብሔር “Diversity”ን የሚያስከብር አይደለም፣
ስለዚህም ፦
ኢትዮጵያ እስከ አሁን ስታራምደው የነበረው ፌዴራላዊ አወቃቀር ሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም አይደለም። በየክልሉ ያሉ የአናሳ ብሔሮችን የዜግነትን መብት በሚቃረን መልኩ ከፖለቲካ ውክልና (በተለይም ከምርጫ ፖለቲካ) እና ከኢኮኖሚ (ከክልሉ ባለቤትነት) እያገለሉና እየነጠሉ “ፌዴራሊዝሙ ሕብረ-ብሔራዊ ነው” ማለት ቀልድ ነው። ይህን ማጠቃለያ የሚጠራጠር ካለ፣ በሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝምም ሆነ በ”Multiculturalism” ፅንሰሐሳቦች ዙሪያ የካናዳዊውን ዊል ኪሚልካ፣ የእንግሊዛዊዉን “Bhikhu Parekh”ን እና የሲንጋፖራዊቷን የ”Terry-Anne Teo”ን መፅሐፍት ያገላብጥ! በነገራችን ላይ ሕንድ ውስጥ ካሉት በሺህዎች ከሚቆጠሩ ብሔሮች መካከል በዋናነት የሦስትና የአራት ያህል አናሳ ብሔሮች መብት ጥያቄ ውስጥ በመግባቱ የሕንድ ፌዴራሊዝም ሕብረ-ብሔራዊ አይደለም ብለው የሚሞግቱ ምሁራን አሉ። እኛ ሀገር በየክልሉ ያልተከበረው የሁሉም ብሔሮች (80+) የዜግነት መብቶች ናቸው።

Read 1407 times
Administrator

Latest from Administrator