Print this page
Wednesday, 08 September 2021 00:00

17,500 የዛፍ ዝርያዎች ከምድረ ገጽ ለመጥፋት ተቃርበዋል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የአየርላንድ ህዝብ ብዛት ከ170 አመታት በኋላ ከ5 ሚሊዮን አልፏል

            በአለማችን ከሚገኙ የዛፍ ዝርያዎች 33 በመቶ ያህሉ ወይም 17,500 የዛፍ ዝርያዎች ከምድረ ገጽ የመጥፋት አደጋ እንደተጋረጠባቸው ከሰሞኑ የወጣ አንድ ጥናት አስጠንቅቋል፡፡
ቦታኒክ ጋርደንስ ኮንሰርቬሽን ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው የጥናት ውጤት እንደሚለው፣ ዝርያቸው ሊጠፋ የተቃረቡ ዛፎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉ አእዋፍት እና አጥቢዎችን ጨምሮ ህልውናቸው አደጋ ላይ የወደቁ እንስሳት ዝርያዎችን ቁጥር አሳድጎታል፡፡
በርካታ ቁጥር ያላቸው የዛፍ ዝርያዎች ለመጥፋት የተቃረቡባት ቀዳሚዋ የአለማችን አገር ብራዚል ናት ያለው ጥናቱ፣ በአገሪቱ 1 ሺህ 788 የዛፍ ዝርያዎች ለመጥፋት መቃረባቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ፣ የአየርላንድ አጠቃላይ የህዝብ ብዛት ከ170 አመታት በኋላ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ5 ሚሊዮን ማለፉን የአገሪቱ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ቢሮ ባለፈው ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ዩፒአይ አስነብቧል፡፡
ቢሮው ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ የአየርላንድ አጠቃላይ የህዝብ ብዛት ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ 5.01 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የህዝብ ቁጥሩ ከ5 ሚሊዮን ሲያልፍ እ.ኤ.አ ከ1851 ወዲህ ይህ የመጀመሪያ ጊዜው ነው፡፡

Read 11725 times
Administrator

Latest from Administrator