Saturday, 28 August 2021 14:35

ለምን እንዲህ ራስ ምታት ሆነባቸው??

Written by  ደረጄ አሰፋ
Rate this item
(0 votes)

   ለየመንና ሊቢያ እንኳን የተባበሩት መንግስታት (UN) እንዲህ አልተሰበሰበም። የኢትዮጵያ ጉዳይ እንዲህ ለምን ራስ ምታት ሆነባቸው? ብላችሁ ጠይቁ! ጉዳዩ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ስለሆነ ነው። የኛ ማንሰራራት፣ የነጭ ታዛዥ አሽከር አንሆንም ማለት፣ ከባሪያ ንግድ ጀምሮ የተዘረጋውን የምዕራባውያን ስውር ቀንበር የሚሰብር ኃይል ነው። ኢትዮጵያ የእውነት፣ የማንነት፣ የነፃነት፣ የእምነትና እኩልነት መፍለቂያ ሆና ለዘመናት ኖራለች፣ ከኛ በላይ ይህን እውነት ጠንቅቀው ያውቁታል። በታሪክ፣ ጂኦግራፊና ፖለቲክስም ቁልፍ ሚና አላት። ባጭሩ የኢትዮጵያ መንቃት የአፍሪካ መንቃት መነሻ ነው።
ይሄ በውሸትና አፍሪካውያንን በመበዝበዝ ላይ የተመሰረተ “ዘመናዊ” የእነአሜሪካ ኃያልነት በእነ ቻይናና ሩሲያ ፉክክር ገጥሞታል። አፍሪካውያን ራሳቸውን ችለው የቆሙ እለት ደግሞ ያበቃለታል። እናም እንደ ቆሌ የሚያንቀዠቅዣቸው ይሄ ፍርሃት ነው። አሁንም ደግሜ የምነግራችሁ ሙሉ የኢትዮጵያ ህዝብ እምሽክ ቢል UN ደንታው አይደለም። እንዳንሸወድ። አንድነታችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ይጠንክር!!!!


Read 1386 times