Saturday, 28 August 2021 14:33

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   "ችግሩን ለመፍታት የኢትዮጵያ መንግስት በቂ ነው!"
                                         ደጀኔ አሰፋ


                    ወዳጅ ሃገራት ዛሬ ነሐሴ 20 ቀን 2013 በፀጥታው ምክር ቤት ያስተጋቡት ድምፅ፡-
••••••
አባት ሃገር ራሽያ ቃል የለንም!!! በቃ ዝም ብለናል!!
እህት ሃገር ቻይና ውለታሽን ለመመለስ ያብቃን!!
ወዳጅ ሃገር ህንድ ያደረግሽውን አንረሳውም!!
ወዳጅ የሰጠን የኢትዮጵያ አምላክ የተመሰገነ ይሁን!! ኢትዮጵያ ብቸኛ አይደለችም!! ኢትዮጵያ አትረሳውም!!
ኬንያ እንዳለች አይቆጠርም!! አፍሪካዊ ስትሆን ያኔ እንገናኛለን!! ከቅኝ ግዛት ነፃ ስትወጣ እናወራለን!!
እንኳንም ጆሞ ኬንያታ ያልኖሩ!!! ለኡሁሩ አዘንኩ!!
ዛሬ .... የአሜሪካ ሸፍጥ ተደፍቋል!!
የእንግሊዝ ሴራ መና ቀርቷል!!
አሜሪካ ብቻዋን ቆማ እራቁቷን ቀረች!!
እንግሊዝ ክፋቷን ይዛ ተቁለጭልጫ ቀረች!!
ጌታቸው ረዳ፣ ባይደን ያድንህ እንደሆን ዛሬ ተናገር!!
ጁንታው ህፃናትን ለጦርነት መማገዱን ግፍና ሰቆቃ መፈፀሙን፣  የተኩስ አቁም ስምምነትን መግፋቱን፣ አማራና አፋር ክልሎችን መውረሩ... በአጠቃላይ በአሜሪካ ቀሚስ ስር ለወራት የተደበቀው የጁንታው ግፍ እና ወንጀል ተጋለጠ!!
 እውነት አሸነፈ!!!
አሜሪካም እንግሊዝም ጁንታውም በፀጥታው ምክር ቤት ተወቀጡ!! ተሸከሸኩ!! ፈጣሪ በወዳጆቻችን በኩል አሳፈራቸው!! ረፈረፋቸው!! ከእውነት ጋር ተጣልተዋልና ያፍራሉ!! ገና ይሸማቀቃሉ!! ኢትዮጵያ እያሸነፈች እየጎመራች ትቀጥላለች!! ተመስገን!!
“በዚህ ጊዜ ከኢትዮጵያ ጎን የቆማችሁ ሃገራትን አመሰግናለሁ!! በአንፃሩ ጫና እናድርግ የምትሉና “ነገሽን ልወስንልሽ” የሚሏት ሃገራት ግን ሃገሬ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ የነፃነት ታሪክ ያላት ናት!! እሴትና ሞራል ያላት ሃገር ነች!! ማንም ጫና ስላደረገብን ወይም ጉዳዩን ሴንሴሽናል በማድረግ አይሆንም!! ለህዝባችን መደረግ የሚገባውን ነገር እናውቃለን!! የውጭ ጫናን የሚቀበል አንዲትም ኢትዮጵያዊት_ነፍስ እንደሌለች ካለፈው ተምራችሁ አሁን ትክክለኛውን ትምህርት ብትወስዱ እመክራችኃለሁ!!” ብሏቸዋል - የኢትዮጵያ ልጅ፣ ታዬ አፅቀስላሴ - ለአሜሪካ ለእንግሊዝና መስሎቻቸው....
አሁን በዓለም አደባባይ .....
ቅቡልነትና አቅም ያለው መንግስት እንዳለን ወዳጆቻችን መስክረዋል!! ችግሩን በራሳችን እንደምንፈታው ተነግሯል!! በሰብአዊ እርዳታ ስም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት መዳፈር ክልክል ነው ብለዋል!! ከኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ጎን መሆናቸውን ደግመው ደጋግመው አረጋግጠዋል!! ሌሎችም ከኢትዮጵያ ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል!! ዶክተር አብይ አሻንጉሊት መንግስት ስላልሆነላቸው፣ ለጊዜው ምጣችን ቢበዛም ዘለቄታዊ ጥቅማችን፣ ታሪካዊ የነፃነት ክብራችንና ሉዓላዊነታችን ተከብሮ ለዘላለም እንዲኖር ስለሚሆን የወቅቱን ፈተና እንደ ሙሉ ደስታ እንቆጥረዋለን!! አብቹ በርታ!! የምወድህ የሃገሬ ህዝብ በርታልኝ!! የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነቱን ማስጠበቁ ለዛሬው ውጤት ማማር ሚናው የትየለሌ ነው!! አንድ ስንሆን ወዳጆቻችን ደስ ይላቸዋል!! ጠላት ይዋረዳል!! ጉልበታችን ያይላል!! አሁንም እንቀጥል!! አንድ እንሁን!! እንበርታ!! እንያያዝ!! መጭው መስከረም ለኢትዮጵያውያን ልዩ ነው!! በጣም ደስ ብሎኛል!! ደስስስስ ይበላችሁ!! የኢትዮጵያ አምላክ ዛሬም የተመሰገነ ይሁን!! ወዳጆቻችን ይባረኩ!! ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!



Read 2342 times