በመላው አለም እስከያዝነው ሳምንት አጋማሽ ድረስ ከ5 ቢሊዮን በላይ የኮሮና ክትባቶች ለተጠቃሚዎች መሰጠታቸው ቢዘገብም፣ ብሩንዲ፣ ኤርትራና ሰሜን ኮርያ ገና አሁንም ድረስ የክትባት መርሃግብር አለመጀመራቸው ተነግሯል፡፡
እስካሁን በአለማቀፍ ደረጃ ከተዳረሰው 5 ቢሊዮን በላይ የኮሮና ክትባት ውስጥ ወደ ግማሽ የሚቃረበው ወይም 1.96 ቢሊዮን ያህሉ በቻይና መሰጠቱን የዘገበው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ ህንድ 589 ሚሊዮን፣ አሜሪካ ደግሞ 363 ሚሊዮን የኮሮና ክትባቶች የተሰጡባቸው ተከታዮቹ የአለማችን አገራት መሆናቸውንም አመልክቷል፡፡
ካላቸው አጠቃላይ የህዝብ ቁጥር አንጻር ብዛት ያላቸውን ሰዎች በመከተብ ደግሞ፣ ከአለማችን አገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ኡራጓይና እስራኤል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውን አመልክቷል፡፡
Sunday, 29 August 2021 00:00
በአለማችን ከ5 ቢ. በላይ የኮሮና ክትባቶች ቢሰጡም፣ በ3 አገራት ክትባት አልተጀመረም
Written by Administrator
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል