Print this page
Saturday, 28 August 2021 14:06

ኮፐንሃገን በደህንነት ከአለማችን ቀዳሚዋ ከተማ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በመላው አለም የሚገኙ ከተሞችን አጠቃላይ ሁኔታ በመገምገም በየሁለት አመቱ የደህንነት ሁኔታ ደረጃ የሚሰጠው የኢኮኖሚስት መጽሄት የምርመራ ክፍል፣ ሰሞኑን ባወጣው የ2021 አመት ሪፖርቱ የዴንማርክ መዲና ኮፐንሃገንን በደህንነት አቻ የማይገኝላት የአለማችን ከተማ ሲል በአንደኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡
የጤና ደህንነት፣ የመሰረተ ልማት ደህንነት፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ደህንት፣ የግለሰባዊ አኗኗር ደህንነትና የአካባቢ ደህንነት በሚሉ አምስት ዋነኛ ማንጸሪያዎች በ76 መስፈርቶች ተጠቅሞ የ60 ታላላቅ የአለማችን ከተሞችን አጠቃላይ ሁኔታ ገምግሞ ደረጃ የሰጠው ተቋሙ ከሰሞኑ ባወጣው አዲስ ሪፖርቱ እንዳለው፣ ኮፐንሃገን 82.4 ነጥብ ከ100 በማምጣት ነው አንደኛ ደረጃን ለመያዝ የበቃችው፡፡
የካናዳዋ ቶሮንቶ፣ የሲንጋፖር ሪፐብሊኳ ሲንጋፖር፣ የአውስትራሊያዋ ሲድኒና የጃፓኗ ቶኪዮ እንደቅደም ተከተላቸው ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን ከተሞች ሲሆኑ፣ አምስተርዳም፣ ዌሊንግተን፣ ሆንግ ኮንግ፣ ሚልበርንና ስቶክሆልም እስከ አስረኛ ደረጃ ለመያዝ ችለዋል፡፡
በአንጻሩ ደግሞ በሪፖርቱ ከተካተቱ የአለማችን ከተሞች መካከል በደህንነት እጅግ አነስተኛውን ደረጃ የያዘችው የናይጀሪያዋ ሌጎስ ስትሆን፣ ካይሮ፣ ካራካስ፣ ካራቺና ያንጎን ይከተሏታል፡፡


Read 1219 times
Administrator

Latest from Administrator