Sunday, 22 August 2021 13:08

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ጸሐይ ከንፈር አላት፥ እንጆሪ ሚመስል
ጨረቃ ጣት አላት፥ ቀጭን እንዳለንጋ
ሰማይ አለው እሳት፥ ምድርን የሚያከስል
ከጥጥ የተሰራ፥ ደመና አለው አልጋ።
ተራራ አንገት አለው፥ መቃ የመሰለ
አለቱ ሕብስት ነው፥ በጣይ የበሰለ
ዛፍ አለው ቁንዳላ፥ የተመሳቀለ
ድንጋይ ብርሃን አለው፥ የተንቀለቀለ
ጨለማ ግርማ አለው፥ እጅግ ሚያንፀባርቅ
ሰይጣን እምነት አለው፥ ከእግዜር የሚያስታርቅ
ሰው ባለግብር ነው፥ መልዓክ ሚተካከል
ብሳና ወይን ነው፥ ገነት የሚተከል።
ይኼ ነገር…
እንዴትም ብታስብ፥
የማይሆን ነው ብለህ እንዳትሞግተኝ
እንዴት ሆነም? ብለህ፥
ምስጢር እንዳወጣ እንዳትወተውተኝ።
የማይሆነው ሁሉ፥
ታምራቱ ሁሉ
በኢምንት ልኬት፥ ፊቴ የሚፈፀም እየተሰፈረ
ታምርን ያደርጋል፥ ፍቅሬ አፍቅሩ አንሶ፥ እግዜር እያፈረ።
ሳስብህ ይሆናል፥ ይኼ ሁሉ ታምር
ና ላሳይህ አንዴ፥ (ሚወደንን ሳይሆን፥)
ሚጠላንን ማፍቀር፥ እንዴት  እንደሚያምር
    ከዳግም ሕይወት

___________________


         ነጭ ገደል ሰካራም

ቅጂልኝ!
ትርፍ እማታሳዪ
ደንበኛ ‘ማትረሺ
አንቺ ቸር ኮማሪት፤
ሲሻሽ በሽክናሽ
በጅ ካልሽም በገንቦሽ።
እኔማ -’ንኮላሽ ነኝ
እኔማ ነጭ ገደል
ሰካራም ገደል ነኝ፤
ባንቆረቆርሽልኝ ቁጥር
መሞላት ‘ማይበቃኝ
ከስንቅነህ እሸቱ (ኦ ‘ታም ፑልቶ)


Read 2060 times