ባለፈው የፈረንጆች አመት 2020 ብቻ በአፍሪካ አህጉር 30 ሺህ የሚጠጉ ህጻናት በካንሰር ሳቢያ ለሞት መዳረጋቸውን የአለም የቴና ድርጅት ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ ካንሰርን ጨምሮ ለሌሎች በሽታዎች የሚደረጉ ህክምናዎችን በማስተጓጎል ከፍተኛ ጥፋት ማስከተሉን ያስታወሰው ድርጅቱ፣ በአፍሪካ ከሚገኙት አገራት በ46 በመቶው የህጻናት ካንሰር ምርመራ መስተጓጎሉን አመልክቷል፡፡
በአፍሪካ የካንሰር ህክምና የሚያገኙ ህጻናት 30 በመቶ ያህሉ ብቻ መሆናቸውንና በህጻናነት ካንሰር የመሞት ዕድል በአፍሪካ 80 በመቶ ብቻ መሆኑን የጠቆመው ድርጅቱ፣ በከፍተኛ ገቢ አገራት ግን 20 በመቶ ብቻ መሆኑን አክሎ ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ