Print this page
Saturday, 14 August 2021 14:07

በኮመርስ ከቦታው መነሳት ጉዳይ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

       ዶ/ር  ወርቁ መኮንን ኮመርስ (የንግድ ሥራ ኮሌጅ) ከቦታው መነሳቱን በመቃወም፣ በሪፖርተር ጋዜጣ ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም የተወሰኑ ውሀ የማይቋጥሩ ነጥቦችን አስቀምጠዋል።
መነሳታቸው አግባብነት ያለውና መንግስት ወደፊትም በሌሎችም በጥናት ላይ ተመስርቶ እንዲያድሱ፣ ደረጃውን የጠበቀ ህንፃ እንዲገነቡና ቦታ እንዲቀይሩ ማድረግ ይጠበቅበታል። ይህም አዲስ አበባን፣ አዲስ አበባ የማድረግ ወሳኝ ተግባር ሲሆን እንደ ኮመርስ ያሉ ተቋማት ላይ ግን የተወሰደው እርምጃ ቢዘገይም ትክክለኛነቱን መጥቀስ ያስፈልጋል።
1.ተቋሙ እንደ ስሙ እድሜውና የያዘው ትልቅ ስፍራ የቆሻሻ መጣያ የመሰለ፣ ውስጡና ውጭው የቆሸሸ፣ ገፅታን የሚያበላሽ፣ ለተማሪው የማይመጥን አሳፋሪ ስፍራ የነበረ መሆኑ ያደባባይ ሚስጢር ነው።
2. አዲስ አበባ በጀመረችው የከተማ ለውጥ ጉዞ (አርባናይዜሽን) ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ፣ የከተማችንን ውበት እውን ማድረግ በሁለንተናዊ ቅንጅታዊ ስራ በመሆኑ፣ የረባ ያልረባ ምክንያት መፍጠር ሳይሆን የመፍትሄ አካል መሆን ይገባል።
3.  ለውጥ ሲኖር ነውጥ መኖሩ ግር ሳይለው በቀጣይም መንግስት ከተማዋን ለማዘመን የሚታደሱ፣ የሚፈርሱ ብሎም የሚሸጋሸጉ ተቋማት መኖራቸውን የቅድመ ግንዛቤ ስራ በመስራት፣ ኢትዮጵያን የአለም ቱሪስቶች ግንባር ቀደም መስህብ ማድረግ ያስፈልጋል።
ስዩም አበረ
( PhD in Urban Planning )


Read 2079 times
Administrator

Latest from Administrator