Tuesday, 03 August 2021 18:31

“የክስታኔ ጉራጌ ጎርደና ሴራና ተያያዥ ባህሎች” መፅሐፍ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

በዶ/ር ፍቃዱ ደስታ አሪፎ የተፃፈ “የክስታኔ ጉራጌ” ጎርደና ሴራ እና ተያያዥ ባህሎች የተሰኘ የክስታኔ ጉራጌ ማህበረሰብ ላይ መሰረት ያደረገ መፅሐፍ ነሐሴ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል።
እንዲሁም  እሁድ ነሐሴ 2 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ በ4፡00 ሰዓት በቡኢ ከተማ ይመረቃል። መፅሐፉ የክስታኔ ማህበረሰብ የዛሬ 800 ዓመት አካባቢ የነበረውን የፍትህና የዳኝነት ስርዓት የሚያስቃኝ ሲሆን ባህላዊ ህጉ አሁን ካለው ዘመናዊ ህግ ጋር በማያያዝ ቢሰራበት  እንደሚጠቅም ያመለክታል። ሌሎችም የማህበረሰቡ ባህሎችን አካትቶ ያቀረበ ጥናታዊ መጽሐፍ ነው-ተብሏል። በምረቃ ስነ-ስራዓቱ ላይ ዶ/ር ወዳጄነህ ማህረነ፣ ዶ/ር ዓለማየሁ ግርማ ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕለ፣ ዶ/ር ዳንኤል ተመስገን በመፅሐፉ ዙሪያ ሃሳባቸው ያጋራሉ። በዕለቱ ሌሎች ምሁራንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችም ይታደማሉ።  

Read 6687 times Last modified on Wednesday, 04 August 2021 20:20