Tuesday, 03 August 2021 17:27

“ያየን የለም እንጂ ያላየነው የለም” አለ ወያላ!

Written by  ዘውድአለም ታደሠ
Rate this item
(0 votes)

   (አማን መዝሙር)
ዘንድሮ መቼስ ያላየነው የለም። ቅድም በቴሌቭዥን በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች እጅግ ብዙ ለመዝመት የተሰበሰቡ ወጣቶች በጥላሁን ገሰሰ «እናት ሐገር ኢትዮጵያ» በሚለው ዘፈን እየዘለሉ ሲጨፍሩ አይቼ ገረመኝ። ኸረ የኢትየጵያን ባንዲራ አቅፎ የሚያለቅስ ቄሮ (ያው ወጣት ሁሉ ቄሮ ነው) አየሁና ለመጀመሪያ ጊዜ የገዛ ህዝቤን እንደማላውቀው ተሰማኝ!
መቼስ ይሄ ሁሉ ወጣት ተከፍሎት ነው ወይም አስፈራርተውት ነው የዘመተው ለማለት ይከብዳል። እሺ አስፈራርተውት ይዝመት፣ አስፈራርተውት ግን በጥላሁን ገሰሰ ዘፈን ልቡ እስኪጠፋ አይጨፍርም
ብቻ በዚህ ሶስት አመት ያላየነው ነገር የለም። ነገሮች እንደ ሰርከስ ትግራይ ሲገለባበጡ አይተናል።
ባለፈው ስታሊን የሚባል የህውሓት Gifted ውሸታም አለ። ውሸት በማን ያምራል ብትሉኝ በስታሊን እላችኋለሁ። በቃ ተፈጥሯዊ ውሸታም ነው። ታለንትድ ነው። የሚዋሸውን ነገር መጀመሪያ ራሱ አምኖት ነው እሚዋሸው። መዝናናት ስፈልግ እሱን ነው እማየው።
ባለፈው የኢትዮጵያ መከላከያ መቀሌ ሊገባ ሰአታት ቀርቶት ሁሉ ስታሊን በቴሌቭዥን መጥቶ «ለወሬ ነጋሪ ሳናስቀር እየደመሰስን ነው» ይል ነበር። እስከዛሬ ስታሊን የደመሰሳቸው ወታደሮች ብዛት እንኳን ኢትዮጵያ ምስራቅ አፍሪካ ውስጥ የለም። መቶ አስር ሚሊየን ህዝብ ደምስሶ ጨርሶ ከመጪው ትውልድ ሁሉ እየተበደረ ደምስሷል። ናቲና ሙክታሮቪች’ኮ አንዳንዴ ስልታዊ ማፈግፈግም ያደርጋሉ። ስታሊን አያፈገፍግም። የኢትዮጵያ ወታደር መቀሌ ገብቶ ራሱ ስታሊን ብቻውን ቆቦን ተቆጣጥሮ ቆይቷል። አንዳንዴ እንደ ቻርሊ ቻፕሊን ብቻውን አንድ ሜካናይዝድ ጦር ይከብባል። ስታሊን ያልጣለው አውሮፕላንም የለም። ደስ ሲለው እንደውም ሰው አልባ ድሮን በሚሳኤል ይመታና ፓይለቱን ይማርካል ብቻ ልጁ ያዝናናኛል።
እና ይሄ ስታሊን ባለፈው ፕሮፌሰር ህዝቅኤል ጋቢሳ ከተባለ ባጠናው ባጠናው ምን እንደሚፈልግ እስከ ዛሬ ካልገባኝ ሰው ጋር ይወያያል።
እንዲህ አለ ስታሊን፤ «እንደው ግን ቄሮ ምነው ዝም አለ? ለምን ይሄን እድል ተጠቅሞ መንግስትን አያንቀጠቅጥም? ምን ሆኖ ነው ጭጭ ያለው?» ሲል ህዝቅኤል እንዲህ አለ ... «እኔም ግራ የገባኝ እሱ ነው»
እኔን ግራ ይግባኝ ሲመስለኝ ቄሮ ትግሉን ጨርሶ «ትግልህን ጨርሰሃል ወደ ቤት ግባ» ተብሎ ወደ ቤቱ ከገባ ቆየ። በወንድማማች መሃከል ያለ conflict of power አይመለከተውም። ይኸው አሁን ሁሉን ትቶ በጥላሁን ገሰሰ ዘፈን እስክስታ እየወረደ ወደ ጎንደር እየተጓዘ ነው። (እዚች ጋ ፈገግ እንላለን )



Read 1744 times