Print this page
Saturday, 24 July 2021 00:00

ቻይና የአለማችንን እጅግ ፈጣን ባቡር አስመረቀች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ቻይና በአለማችን ታሪክ በፍጥነቱ አቻ አይገኝለትም የተባለውንና በሰዓት 600 ኪሎሜትር የመጓዝ አቅም ያለውን እጅግ ፈጣን ባቡር ከሰሞኑ ኪንዳኦ በተባለው አካባቢ በይፋ ማስመረቋን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡ ማግሊቭ የሚል ስያሜ የተሰጠውና ቻይና ሬልዌይ ሮሊንግ ስቶክ ኮርፖሬሽን በተባለው የአገሪቱ መንግስት ተቋም የተሰራው ይህ እጅግ ፈጣን ባቡር ከተነጠፈለት ሃዲድ ከፍ ብሎ በኤሌክትሮ ማግኔቲክ ስበት አማካይነት እየተንሳፈፈ ሲከንፍ ማየት እጅግ እንደሚያስደምም ዘገባው አስነብቧል፡፡
ባቡሩ ከፍጥነቱ በተጨማሪ የሚያወጣው የድምጽ ብክለት አነስተኛ መሆኑ እንዲሁም ከሌሎች ፈጣን ባቡሮች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ጥገና የሚያስፈልገው መሆኑ ለየት እንደሚያደርገው የጠቆመው ዘገባው፣ በቻይና በስራ ላይ የሚገኙ ፈጣን ባቡሮች በአማካይ 350 ኪሎሜትር በሰዓት የመጓዝ አቅም ያላቸው መሆናቸውም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 951 times
Administrator

Latest from Administrator