Print this page
Tuesday, 20 July 2021 00:00

የሜዲትራኒያን ባህር ስደተኞች ሞት ከእጥፍ በላይ ጨምሯል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፉት ስድስት ወራት የሜዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው ወደ አውሮፓ አገራት ለመግባት ሲሞክሩ በሚያጋጥሟቸው አደጋዎችና ጥቃቶች ለሞት የሚዳረጉ ስደተኞች ቁጥር ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከእጥፍ በላይ መጨመሩን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት ያወጣውን ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ከጥር እስከ ሰኔ በነበሩት ወራት ከ1 ሺህ 146 በላይ የተለያዩ አገራት ስደተኞች በሜዲትራኒያን ባህር ለሞት መዳረጋቸውን ለማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ባህሩን አቋርጠው የተጓዙ ስደተኞች ቁጥርም በ56 በመቶ ያህል ጭማሬ አሳይቷል፡፡
ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ከሞቱባቸው የሜዲትራኒያን ባህር የጉዞ መስመሮች መካከል ከሊቢያ ወደ ጣሊያን የሚወስደው በቀዳሚነት ይጠቀሳል ያለው የድርጅቱ ሪፖርት፣ በዚህ መስመር በድምሩ 741 ስደተኞች ለሞት መዳረጋቸውንም አመልክቷል፡፡
ባለፈው አመት ከኮቪድ ወረርሽኝ የጉዞ ክልከላዎች ጋር በተያያዘ ወደ አውሮፓ አገራት የገቡ ስደተኞች ቁጥር ከ2015 የፈረንጆች አመት ወዲህ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን ያስታወሰው ሪፖርቱ፣ በአመቱ 1 ሚሊዮን ያህል የተለያዩ አገራት ስደተኞች በባህር ጉዞ ወደ አውሮፓ መግባት መቻላቸውንና አብዛኞቹም የሶርያ ስደተኞች መሆናቸውን ገልጧል፡፡

Read 2603 times
Administrator

Latest from Administrator