Print this page
Saturday, 17 July 2021 14:27

አምነስቲና ኢሰመኮ በትግራይ ተወላጆች ላይ የሚደርስ ህገወጥ እስርና ጥቃት በአፋጣኝ እንዲቆም አሳሰቡ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከትግራይ ግጭት ጋር ተያይዞ በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርስ እንግልት፣ ከሕግ አግባብ ውጪ የሆነ እስርና ጥቃት በአፋጣኝ ሊቆም እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን አምነስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ፤  በትግራይ ተወላጆች፣ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ከሕግ አግባብ ውጪ የሆነ እስር እንዲቆም ጠይቋል።
ኢሰመኮ፤ በሲቪል ሰዎች ላይ እንግልትና እስር፣ ጥቃት እንዲሁም  የንግድ ቤት መዘጋት መከሰቱንና ሕይወት መጥፋቱን የጠቀሰው ኢሰመኮ፤በእስረኞችና በምርኮኞች ላይ የሚደርስ ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ፣ በስደተኞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና ሕጻናትን ለውትድርና መጠቀምን የሚያመላክቱ መረጃዎች እጅግ እንደሚያሳስበው አመልክቷል።
ኮሚሽኑ ሐምሌ 4 ቀን 2013 ዓ.ም በደቡብ ጎንደር ዞን፣ ፎገራ ወረዳ፣ ወረታ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ሦስት የትግራይ ተወላጆች በድንገት በተሰባሰቡ ነዋሪዎች በደረሰባቸው ድብደባ መገደላቸውን  መረጃ ደርሶኛል ብሏል።
አምነስቲ ኢንተርናሽል በበኩሉ፤#የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ የትግራይ ተወላጆችን ከሕግ አግባብ ውጪ በሆነ መልኩ አስሯል; ሲል መግለጫ አውጥቷል።
በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም ታስረው እንደሚገኙ የጠቆመው አምነስቲ፤ መንግሥት ከሕግ አግባብ ውጪ የሆነ እስርን እንዲያቆምና አሁንም ከሕግ አግባብ ውጪ የታሰሩትን በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቅ ጠይቋል።
የፌደራል ፖሊስ በበኩሉ፤ “ሰዎች በወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ሊውሉ ይችላሉ፤ ይሁን እንጂ ማንም ሰው ማንነቱን መሠረት ባደረገ መልኩ ለእስር አልተዳረገም” ሲሉ አስተባብለዋል፡፡

Read 14594 times
Administrator

Latest from Administrator