Print this page
Tuesday, 29 June 2021 00:00

9% የአለም ህዝብ በችግር

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ምክንያት እራት እንደማይበላ ተነገረ
በመላው አለም 41 ሚሊዮን ሰዎች ለከፋ ረሃብ ተጋልጠዋል ተባለ

ከአጠቃላዩ የአለማችን ህዝብ ወደ 9 በመቶ የሚጠጋው ወይም 690 ሚሊዮን ያህል ሰዎች በየዕለቱ ለራት የሚሆን ምግብ ማግኘት ባለመቻላቸው ሳይበሉ እንደሚተኙ የገለጸው የአለም የምግብ ድርጅት፣ በ43 የአለማችን አገራት ውስጥ የሚገኙ 41 ሚሊዮን ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸውን አስታውቋል፡፡
በአራት የአለማችን አገራት ውስጥ የሚገኙ ተጨማሪ 600 ሺህ ያህል ሰዎች ከረሃብ ባልተናነሱ አደገኛ ሁኔታዎች ውስጥ የከፋ ኑሮን እየገፉ እንደሚገኙ ባለፈው ማክሰኞ ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርት ያስታወቀው ድርጅቱ፣ በአለም ዙሪያ የረሃብ አደጋ ያንዣበበባቸውን 41 ሚሊዮን ሰዎች ለመታደግ 6 ቢሊዮን ዶላር ያህል የአፋጣኝ እርዳታ ድጋፍ እንደሚያስፈልግም አስጠንቅቋል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ ለረሃብ የተጋለጡ ሰዎች ቁጥር ለረጅም አመታት ሲቀንስ ቢቆይም ላለፉት አምስት አመታት መጨመር ማሳየቱን ያስታወሰው ድርጅቱ፤ ጦርነቶች፣ የአየር ንብረት ለውጥና የኢኮኖሚ ቀውሶች የሸቀጦች ዋጋ መናርንና የርሃብ አደጋዎችን የጨመሩ ምክንያቶች መሆናቸውን የጠቆመ ሲሆን፤ ባለፈው አመት ደግሞ የኮቪድ ወረርሽኝ ሁኔታውን ክፉኛ እንዳባባሰውና የምግቦች ዋጋ ባለፈው ግንቦት ወር ላይ በአስር አመት ውስጥ ከፍተኛው ሆኖ መመዝገቡን አስረድቷል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ድርጅት በበኩሉ ባለፈው ሰኞ ባወጣው አለማቀፍ መረጃ፣ በአለማችን በአስገዳጅ ሁኔታ ከመኖሪያ አካባቢያቸው ተፈናቅለው ለመሰደድ የተገደዱ ሰዎች ቁጥር 82 ሚሊዮን መድረሱንና ከአጠቃላዩ የአለማችን ህዝብ 1 በመቶ ያህሉ በመሰል ሁኔታ ተፈናቅሎ እንደሚገኝ ማስታወቁን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
ባለፈው የፈረንጆች አመት 2020 ብቻ በመላው አለም 11.2 ሚሊዮን ያህል ሰዎች በአስገዳጅ ሁኔታ ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን የጠቆመው ድርጅቱ፣ በርካታ ቁጥር ያላቸው ተፈናቃዮችን ለስደት ከዳረጉት ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል ግጭት፣ አመፅና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንደሚገኙባቸውም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 962 times
Administrator

Latest from Administrator