የአፍሪካ አየር መንገዶች ከኮሮና ቫይረስ ቀውስ ጋር በተያያዘ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2020 በድምሩ የ10.21 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንዳጋጠማቸው የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማህበር ከሰሞኑ ባወጣው አመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
የአፍሪካ የአየር መንገዶች በ2020 የፈረንጆች አመት ያጓጓዟቸው መንገደኞች ቁጥር በ2019 ከነበረበት በ63.7 በመቶ ቅናሽ በማሳየት 34.7 ሚሊዮን መድረሱን የማህበሩ ሪፖርት የጠቆመ ሲሆን በአመቱ ከአፍሪካ አየር መንገዶች መካከል በአገር ውስጥ፣ በአህጉራዊና በአለማቀፍ በረራዎች በድምሩ በርካታ ቁጥር ያላቸውን መንገደኞች በማጓጓዝ ቀዳሚነቱን የያዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲሆን፣ ኢጅፕትኤር፣ ሮያል ኤር ሞሮኮ፣ ሳፋሪና ኬንያን ኤርዌይስ ይከተላሉ፡፡
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት በበርካታ የአለማችን አገራት የጉዞ ክልከላዎችን በማድረጋቸውና የጉዞና እንቅስቃሴ ገደቦች በመጣላቸው ሳቢያ፣ የአለማችን ስድስቱ ግዙፍ አየር መንገዶች በአመቱ በድምሩ 110 ቢሊዮን ዶላር ያህል ኪሳራ እንዳጋጠማቸውም ዘገባው አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል