አለማችን ከአንድ አመት በላይ አሳር መከራዋን ሲያሳያት የከረመውንና አሁንም በእጅግ ከፍተኛ ፍጥነት በመሰራጨት ላይ የሚገኘውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በወራት ጊዜ በቁጥጥር ስር ማዋል እንደምትችል የገለጸው የአለም የጤና ድርጅት፤ ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አስፈላጊ ሃብቶችን በፍትሃዊነት መከፋፈል ሲቻል ብቻ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
የድርጅቱ ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በሳምንቱ መጀመሪያ በሰጡት መግለጫ፤ ኮሮናን በቀጣዮቹ ወራት በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያስችሉ መሳሪያዎች ቢገኙም የአለማችን አገራት እነዚህን መሳሪያዎች በፍትሃዊነት መከፋፈልና በዘላቂነት መጠቀም ካልቻሉ ግን ቫይረሱን በቁጥጥር ስር ማዋል አይቻልም ማለታቸውን የዘገበው ሮይተርስ፤ የተገኘው መላ ምን እንደሆነ ግን በግልጽ አልተናገሩም ብሏል፡፡
ቫይረሱ አሁንም በመላው አለም በእጅግ ከፍተኛ ፍጥነት በመሰራጨት ላይ እንደሚገኝና በተለይ ከ25 እስከ 59 አመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሰዎችን እያጠቃ እንደሚገኝ ያልሸሸጉት ዳይሬክተሩ፤ በፍጥነት ለመሰራጨቱ በምክንያትነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት ጉዳዮች መካከል የቫይረሱ አዳዲስ ዝርያዎች በብዛት መፈጠራቸው አንዱ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል