Thursday, 11 March 2021 00:00

አይስላንድ በ1 ሳምንት ብቻ 17 ሺህ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶባታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    ባለፈው ሳምንት ብቻ በአይስላንድ ባልተለመደ ሁኔታ እጅግ በርካታ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች መፈጠራቸውንና በሳምንቱ በአገሪቱ ደቡብ ምዕራባዊ ሪክጃኔስ ግዛት 17 ሺህ ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ  መፈጠራቸውን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
አገሪቱ ምንም እንኳን ለመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ ባትሆንም በዚህ መልኩ በአጭር ጊዜ በርካታ ክስተት ሲፈጸም ግን ይህ የመጀመሪያው ነው ያለው ዘገባው፤ ከፍተኛው ረቡዕ ዕለት የተከሰተውና በርዕደ መሬት መለኪያ 5.6 የተመዘገበው እንደነበርም አስታውሷል፡፡
በተከታታይ ቀናት ሌሎች የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች በፍጥነት መፈጠራቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ከክስተቶቹ ብዛት አንጻር ያን ያህል የከፋ ጉዳት አለመድረሱንም አክሎ ገልጧል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች ክስተቱ ያልተለመደ መሆኑን ጠቅሰው፣ ሳምንቱን ሙሉ መሬት ከጧት እስከ ማታ ስትንቀጠቀጥ መመልከት ራስን ከተፈጥሮ መከላከል የማይችል ቅንጣት አቅም የለሽ ፍጡር አድርጎ የመቁጠር ስሜትን ይፈጥራል ማለታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 4918 times