Tuesday, 16 February 2021 00:00

በአለም 2ኛው የቢራ ኩባንያ ሄኒከን 8 ሺ ሰራተኞቹን ሊቀንስ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ከኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር በተያያዘ ሽያጩ በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰበት የአለማችን 2ኛው ግዙፍ የቢራ አምራች ኩባንያ ሄኒከን ወጪውን ለመቀነስ ሲል በተለያዩ የአለም አገራት ውስጥ ከሚገኙ ሰራተኞቹ 10 በመቶ ያህሉን ወይም 8 ሺ የሚደርሱ ሰራተኞቹን ከስራ ሊያሰናብት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ በፈረንጆች አመት 2019፣ 2.2 ቢሊዮን ፓውንድ ትርፍ ያስመዘገበው  ሄኒከን፣ በ2020 ግን ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ አጠቃላይ ሽያጩ በ17 በመቶ በመቀነስ ትርፉ ከአምናው በ204 ሚሊዮን ፓውንድ መቀነሱን ያስታወሰው ዘገባው፣ ኩባንያው ሰራተኞቹን መቀነስን ጨምሮ የተለያዩ የወጪ ቀነሳ እርምጃዎችን በመውሰድ በ3 አመታት ጊዜ ውስጥ 2 ቢሊዮን ፓውንድ ለማዳን ማቀዱን አመልክቷል፡፡

Read 2645 times