ያንቺን ድምፅ ብቻ፣ ሲያቃጭል የኖረ
የቆለፍሺው ጆሮ፣ በምን ተሰበረ?
ይኸው ብዙ ድምፆች
ከየትም እየመጡ፣ ይሰሙኝ ጀመረ።
የዘጋሽው ልቤ!
የቆለፍሽው ልቤ!
የተሰባበረው
እንዴት ሰው አማረው?
። ። ።
ልረሣሽ ነው መሠል፣ ወይ ደግሞ
ልትመጪ
ይሰማኝ ጀመረ
ያውደኝ ጀመረ
ይታየኝ ጀመረ፣ ሕይወት ካንቺ ውጪ።
(በላይ በቀለ ወያ)
__________________
የዕድሜ ልክ ደብዳቤ
ይድረስ ለምወድሽ…
ዓለም ያክል ሐሳብ የተሸከመ ሰው፣
ዕረፍት አያገኝም ፍቅር ቢዳብሰው።
ቢሆንም እውነታው፣
ሞቴ አንች ነሽና…!
Published in
የግጥም ጥግ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል