በጋዛ ከአየር ላይ ውሃ መስራት ተችሏል
የሲንጋፖር ናሽናል ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች፣ ከሰው ልጆች ሰውነት ከሚወጣው ላብ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት የሚያስችል አዲስ የምርምር ውጤት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ይፋ ያደረጉትን መረጃ ጠቅሶ የአገሪቱ መንግስት ድረገጽ እንደዘገበው፣ አዲሱ የምርምር ውጤት ከሰውነት የሚመነጨውን ላብ በመምጠጥ በአዲስ ዘዴ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት የሚያስችል ነው፡፡
የምርምር ግኝቱ በቤተ ሙከራ ውስጥ ውጤታማ እንደሆነ ቢረጋገጥም፣ በስፋት ስራ ላይ የሚውልበት ጊዜ በግልጽ አለመነገሩን የጠቆመው ዘገባው፣ በአዲሱ መንገድ የሚመነጨው ሃይል ግን አነስተኛ እንደሚሆን መነገሩን አክሎ ገልጧል፡፡
በሌላ ሳይንሳዊ ዘገባ ደግሞ፣ በፍልስጤሟ የጋዛ ግዛት ውስጥ በተጀመረ አንድ ፕሮጀክት በጻሃይ ብርሃን ሃይል በመጠቀም ከአየር ላይ እርጥበትን በቀጥታ በመምጠጥ ጥራቱን የጠበቀ የመጠጥ ውሃ ማምረት መቻሉን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ከሰሞኑ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
ማይክል ሚሪላሺቪ የተባሉት ሩስያ እስራኤላዊው ቢሊየነር ያቋቋሙት ዋተርጂን የተባለ ኩባንያ፣ በጋዛ ያለውን ስር የሰደደ የመጠጥ ውሃ እጥረት ለመቀነስ በማሰብ የጀመረው ይህ ፕሮጀክት፣ በሳይንሳዊ መንገድ ከአየር ላይ በየዕለቱ እስከ 6 ሺህ ሊትር የሚደርስ የመጠጥ ውሃ ለማምረት የሚያስችል እንደሆነ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ኩባንያው በአዲስ መልኩ የመጠጥ ውሃ የሚያመርቱ እያንዳንዳቸው 61 ሺህ ዶላር የሚያወጡ ማሽኖችን ለጋዛ ከተማ በስጦታ መልክ ማበርከቱንና ማህበረሰቡ የውሃ ተጠቃሚ መሆኑንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል