Print this page
Saturday, 09 January 2021 11:36

የህወሓት መሥራች ስብሃት ነጋና ሌሎች አመራሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

        አንጋፋው የህወኃት መሥራችና ቀንደኛ መሪ አዛውንቱ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች የቡድኑ አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የመከላከያ ሰራዊት ገለፀ።
#ላለፉት 27 አመታት የማተራመስ ስትራቴጂ የነደፈ፣ ያስተባበረና ያደራጀ፣ በመጨረሻም ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማድረግ በሀገራችን ሰራዊት ላይ እጅግ ዘግናኝ ጦርነት በመክፈት ሰራዊቱን ያስጨፈጨፈው የጁንታው ቁንጮ፣ ስብሃት ነጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።; ብሏል፤ መከላከያ በመግለጫው፡፡
የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው እንደገለፁት፣ #የጁንታው ቁንጮ አመራር ስብሃት ነጋ ከተደበቀበት ለሰው ልጅ እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ሰርጥ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሏል። የጁንታውን ቁንጮ ስብሀት፣ የጥፋት ቡድኑ አባላት በሰርጡ ውስጥ ተሸክመው በማስገባት ደብቀውት እንደነበር ነው; ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ የተናገሩት፡፡   
የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፌዴራል የፀጥታ አካላት በጋራ ባደረጉት ፍተሻና አሰሳ፣ ከተደበቀበት በማውጣት በቁጥጥር ስር አውለውታል፤ ብለዋል። በተጨማሪም ከመከላከያ የከዱ ሌሎች የቡድኑ አመራሮች፣ ከጁንታው መሪ ስብሃት ነጋ ጋር አብረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ብርጋዴር ጄነራሉ አመልክተዋል። እነዚሁ ከመከላከያ የከዱ የቡድኑ አመራሮች፣ የጁንታውን ታጣቂ ሀይል በማዋጋትና በማሰልጠን እኩይ ዓላማቸውን ለማስፈፀም ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመው፣ በመጨረሻም የጁንታውን አመራር ጥበቃ ሲያስተባብሩ ቆይተው፣ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ገልፀዋል።
እነዚህን የጁንታውን አመራሮች ለመከላከል በአካባቢው ጥበቃ ላይ የነበረ ታጣቂ ሀይልም መደምሰሱን አክለው ተናግረዋል።
በዚሁ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋሉት፣
የህወኃት ቡድን መሪው ስብሃት ነጋ
ሌተናል ኮሎኔል ፀአዱ ሪች- የስብሃት ነጋ ባለቤትና ቀደም ሲል በጦር ሃይሎች ሆስፒተል ሃኪም የነበረች፣ በኋላም በጡረታ የተገለለች
ኮሎኔል ክንፈ ታደሰ- ከመከላከያ የከዳ
ኮሎኔል የማነ ካህሳይ- ከመለካከያ የከዳ
አስገደ ገ/ ክርስቶስ- ከመሃል ሀገር ተጉዞ ቡድኑን የተቀላቀለና ለጊዜው ሃላፊነቱ ያልታወቀ ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን
የሜጀር ጀነራል ሃየሎም አርአያ ባለቤት የነበረችና ኑሮዋን በአሜሪካ አድርጋ የቆየች በኋላም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ወደ ጁንታው ተቀላቅላ የነበረች፣ ወይዘሮ አልጋነሽ መለስ ጁንታውን በመያዝ ኦፕሬሽን ሂደት ውስጥ ለማምለጥ ስትሞክር ገደል በመግባት ህይወቷ ማለፉን ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ገልፀዋል።

Read 12956 times
Administrator

Latest from Administrator