“ካታላን ኢንስቲቲዩት ኦፍ ስፔስ ስተዲስ” የተባለው የጠፈር ምርምር ተቋም፣ ሳይንቲስቶች በማርስ ፕላኔት ላይ “ኑዋ” የተሰኘች ከተማ ለመቆርቆር ዕቅድ ይዘው እየሰሩ እንደሚገኙ ሲጂቲቼን ዘግቧል፡፡
ሳይንቲስቶቹ በማርስ ላይ አዲስ ከተማ ለመቆርቆር የቀረጹትን “ኑዋ ፕሮግራም” የተሰኘ በአይነቱ አዲስ ፕሮጀክት በመጪዎቹ 30 አመታት ጊዜ ውስጥ ለማሳካት ማሰባቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ከተማዋ እስከ 250 ሺህ ነዋሪዎችን የማስተናገድ አቅም እንደሚኖራትም ገልጧል፡፡
የከተማዋን ንድፍ የሚሰራው አልፈርዶ ሙኖዝ የተባለ ታዋቂ አርክቴክት እንደሆነ የገለጸው ዘገባው፣ የከተማዋን አጠቃላይ ግንባታ ለማጠናቀቅ የሚውለውን ወጪ የሚሸፍነው ተቋሙ እንደሆነም አክሎ ገልጧል።
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል