Print this page
Thursday, 29 October 2020 00:00

ኮሮና በከፋ ድህነት ውስጥ የሚኖሩ ህጻናትን ቁጥር በእጅጉ እንደሚጨምረው ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በየአመቱ ግማሽ ቢሊዮን ህጻናት በተበከለ አየር ሳቢያ ይሞታሉ

             በመላው አለም ከሚገኙት አጠቃላይ ህጻናት 16 በመቶው ወይም 356 ሚሊዮን ያህሉ በከፋ ድህነት ውስጥ እንደሚገኙና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የእኒህን ህጻናትን ቁጥር በእጅጉ ይጨምረዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነገረ፡፡
የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ከአለም ባንክ ጋር በመተባበር ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ እንዳለው፣ በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ ህጻናት ቁጥር እስከ 2017 በነበሩት አራት አመታት፣ በ29 ሚሊዮን ያህል የቀነሰ ቢሆንም፣ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ግን ችግሩን በከፋ ሁኔታ ያባብሰዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በተያያዘ ዜና ደግሞ፣ በመላው አለም በተበከለ አየር ሳቢያ በየአመቱ ግማሽ ቢሊዮን ያህል ህጻናት በተወለዱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለሞት እንደሚዳረጉ ከሰሞኑ ይፋ የተደረገውን የ2020 አለማቀፍ የአየር ሁኔታ ሪፖርት ጠቅሶ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡ ባለፈው የፈረንጆች አመት (2019) በአለማችን ከግማሽ ቢሊዮን በላይ ህጻናት በተበከለ አየር ሳቢያ ለሞት መዳረጋቸውን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ ከነዚህም መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑት የእንጨትና ኩበት ጭስን ጨምሮ በቤት ውስጥ በሚፈጠሩ የአየር ብክለቶች ምክንያት ለሞት መዳረጋቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡ በ2019 የፈረንጆች አመት በመላው አለም በድምሩ ከ6.7 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተበከለ አየር ምክንያት ለሞት መዳረጋቸውን ያስታወሰው ሪፖርቱ፣ የተበከለ አየር በአሁኑ ወቅት በአለማችን በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎችን ለሞት በመዳረግ በአራተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ጠቁሟል፡፡

Read 4893 times
Administrator

Latest from Administrator