Tuesday, 06 October 2020 08:01

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 "ሰው አትከተሉ፤ ጥበብን እንጂ"

አሜሪካውያን ባለጸጋዎቹ ቢል ጌትስና ዋረን በፌት፣ በንባባቸው በእጅጉ ይታወቃሉ። ቢል ጌትስ በዓመት እስከ 50 መጽሐፍት ድረስ  ያነባሉ። ማንበብ ብቻ አይደለም፡፡ #ህይወቴንና ስራዬን የለወጡ የኔ ምርጥ መጻሕፍት እነዚህ ናቸው; በማለት ከነጭብጣቸው ጭምር በየሄዱበት ሁሉ ለተማሪዎች፣ ለሰራተኞችና ለባልደረቦቻቸው ያስተዋውቃሉ። ድረ ገጻቸው ተናፋቂ ነው። በዕውቀት ማካፈል የተዋበ እንጂ የአተካራ ገጽ አይደለም።
ባለፈው ወር 90ኛ ዓመታቸውን የደፈኑትና የቢል ጌትስ የቅርብ ወዳጅ የሆኑት ዋረን በፌትም የባሰባቸው የንባብ ቀበኛ ናቸው። “በቀን ለስድስት ሰዓታት ያህል አነባለሁ” ይላሉ፡፡ እንዲህ እንዳሁኑ እርጅና ሳይጫጫናቸው በፊት ከ500 ገጽ በላይ በአንድ ቀን ፉት ያደርነበር። "ሀብቴን የገነባሁት በመጻሕፍት ነው" ሲሉ የንባብን ፋይዳ ደጋግመው ተናግረዋል። ባለጸጋው በፌት ለሌሎች ሲመክሩም፤ “እውነትን ከመጻሕፍት ውስጥ የመፈተሽና የመመርመር ስራ ላይ አተኩሩ እንጂ እከሌ ስለጻፈው እያላችሁ መጽሐፉ ውስጥ ካለው እውነት ይልቅ ሰው አትከተሉ።” ይላሉ። ከሰው ይልቅ ጥበብን ተከተሉ ነው ነገርየው!

Read 2195 times