Saturday, 26 September 2020 00:00

በአለም ሚሊዮኖች ለሕክምና የተዳረጉበት ወረርሽኝ (COVID-19)

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   ‹‹….ልጄ በድንገት ከምሽቱ አራት ሰአት ላይ ይደውል ልኛል፡፡ እኔም …..ሄሎ….ስል ….. እማዬ….እማዬ…ድረሽልኝ…ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ እኔም በምሽት መኪናዬን አስነስቼ እየበረርኩ ከልጄ ቤት ደረስኩ። ….ቤቱ በጭንቅ ተይዞአል፡፡ ….ምንድነው ጉዱ …አልኩ፡፡ ለካስ የልጄ ሚስት እናት ኮሮና በአገር ደረጃ መኖሩ ስለተነገረ እና በይበልጥ ደግሞ በየሆስፒታሉ እና ጤና ጣቢያው ቫይረሱ ሊተላለፍ ስለሚችል ልጄ ወደዚያ አትሄድም…ከቤት መውለድ አለባት። እኔ ማዋለድ የሚያውቁ ሴት አመጣለሁ…እናንተ ግን ከቤት እንዳትወጡ የሚል ትእዛዝ ሰጥተው ሄደዋል … ተባልኩ….፡፡ ልጅትዋ በምጥ ተይ ዛለች። ባለቤትዋን(ልጄ) ….አንተ መኪናህን አስነስተህ ወደ ሆስፒታል አትወስዳትም እንዴ….ስለው… ልጄን ከቤት ይዘህ እንዳትወጣ ብለው ስላስጠነቀቁኝ ፈራሁ ይለኛል። እኔም …ልጅቱን ተነሽ እንሂድ ስላት…እሺ እማማ… ስትለኝ…አማቼ ሳይመጡ ልጅቱን ይዤ ወደጤና ተቋም በረርኩ፡፡ ጤና ጣብያው በተገቢው ሁኔታ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ልጃችንን ሴት ልጅ አሳቀፈልን…››
በ2012 ይህ አምድ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ለንባብ ካላቸው አንዱን ለትውስታ ነበር ያስነበብናችሁ። በ2012 አጋማሽ በወረርሽ ደረጃ በአገራችን መከሰቱ የተነገረለት COVID-19 ዛሬም አለምን እንዳስጨነቀ ይገኛል፡፡ ሕመሙን ለመከላከል ሲባል የወጡ መመሪያዎችን በመ ተግበሩ ረገድ በትክክለኛውም ይሁን በተሳሳተ መንገድ እንደየሰው አረዳድ ብዙዎች ወትሮ ያደርጉት ከነበረው እንቅስቃሴያቸው ስለተገደቡ ለሕይወት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ለማግኘት አለመቻልን የተለያዩ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ በተለይም ወደ ሆስፒታል መሄድን ፈርተው በቤት ውስጥ መውለድን የመረጡ ብዙዎች መሆናቸውን ለመገንዘብ ተችሎአል።
አንዲት ወጣት ወላድ የሰጠችውን አስተያየትም ለንባብ ማለታችን ይታወሳል፡፡
‹‹…ጎረቤቶቼ እንዲህ ነበር ያሉኝ፡፡ ….በጭራሽ ወደ ጤና ተቋም እንዳትሄጂ…ለመውለድ ብለሽ ከዚያ ብትሄጂ በኮሮና ቫይረስ ትያዣለሽ…የሚል ነበር ንግግራቸው፡፡ ይልቁንስ…አሉ ጎረቤ ቶች…ከቤትሽ ብትወልጂ የኮሮና ቫይረስም ሳይይዝሽ በሰላም ልጅሽን ታቅፊያለሽ የሚል ነበር ምክራቸው…እኔ ግን ከባለቤቴ ጋር ተማክሬ ወጤና ጣቢ በመሄዴ የመጀመሪያ ልጄን በሰላም ወልጃለሁ፡፡ በእርግጥ ጎረቤቶቼም ሆኑ ቤተሰቦቼ  ሊጎበኙኝ መምጣት ባለመቻላቸው አዝኛ ለሁ…ግን ደግሞ ለእነሱም ለእኔም ጥንቃቄ በማድረጋቸው ትክክል መሆኑን እረዳለሁ፡፡›› ነበር ያለችው፡፡
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ፡፡ በቤት ውስጥ በባህላዊ መንገድ ልጅን መውለድና ከዚህ ጋር በተያያዘም በሚከሰቱ የጤና ችግሮች ሞቶች እንደሚኖሩ ይገመታል፡፡  
ያልታቀደ እርግዝናን ለመከላከል የሚያስችሉ መከላከያዎችን ለመው ሰድ እንዲሁም ሳይፈለግ የተጸነሰውን ጽንስ ደህንነቱ በተጠበቀ መንገድ ለማቋረጥ የሚያስችሉትን አገልግሎቶች ለመጠቀም ሰዎች በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ወደ ጤና ተቋማቱ ለመሄድ ስለማይደፍሩ ከነችግሩ በቤታቸው መታቀባቸው ውጤቱ አስፈሪ ነው፡፡
በ Covid-19  ምክንያት በአለም አቀፍ ደረጃ ሚሊዮኖች ያልታቀደ እርግዝናን ለማስወገድና ያልታቀደ እርግዝናን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ የእርግዝና መከላከያዎችን ለማግኘት አልቻሉም፡፡
ምንጭ….Guttmacher Institute
ሌላው ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በአለም ላይ የሚስተዋለውና እንደ ትልቅ ችግር የሚቆጠረው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ነው፡፡
ከInternational Food policy Research Institute-- በተገኘው መረጃ Derek Headey እና Marie Ruel እንደሚሉት፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በአለም አቀፍ ደረጃ ለሚኖረው የተመጣጠነ ምግብ እጦት ትልቅ አስተዋጽኦ አለው፡፡ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት በምን ምክንያት ይከሰታል ብለን ስናስብ ይላሉ ባለሙያዎቹ…..
ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በፊት ይሰሩት ከነበረው ስራ መገለል ወይንም ይሰሩት የነበረው ስራ በወረርሽኙ ምክንያት ገቢ የማያስገኝ በመሆኑ እንዲቋረጥ በመሆኑ የገቢ መቀነስ ወይንም መቋረጥ ሲከሰት፤
በኮሮና ቫይረስ ላለመያዝ በተቻለ መጠን በቤት ቆዩ በሚለው መመሪያ መሰረት በተለ ይም ገቢያቸው ዝቅተኛ የሆኑት ሰዎች በቤታቸው ቢቆዩ ለራሳቸው የሚሆን ነገር የማያ ገኙ መሆኑ እና አቅም ያላቸው ሰዎች ደግሞ በቤታቸው በመቆየታቸው ምክንያት ገበያ ዎች ስለሚቀዘቅዙ እና የእለት ፍላጎቶችን ሸጠው የሚጠቀሙ ሰዎች በመቸገራቸው፤
በመንገድ ላይ የሚሸጡ ምግቦችን ደፍሮ የሚገዛቸው ተጠቃሚ በመቀነሱ፤
በትምህርት ቤቶች የትምህርት ስርአቱ ለጊዜው ስለተቋረጠ የምግብ አቅርቦትም አብሮ በመቋረጡ፤ እና በመሳሰሉት ምክንያቶች በተለይም በዝቅተኛ ኑሮ ደረጃ ላይ የሚኖሩ ሰዎች የተመጣጠነ ምግብ ማግኘት ሊያቅታቸው ይችላል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንድ የጤና ተቋማት ከተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ጋር የተያያዘ አገል ግሎት ይሰጡ የነበሩ ከሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረቱ ላይከሰት እንደሚችል ጥናት አቅራቢ ዎቹ ይገልጻሉ፡፡ ለምሳሌም የእርግዝና ክትትል፤የተመ ጣጠነ ምግብ አቅርቦት፤ የህጻናትን ተቅማጥ መከላከልና ድጋፍ ማድረግ በተመለከተ በሚዘረጉ ፕሮግራሞች፤ኢንፌክሽን፤እና የተ መጣጠነ ምግብ እጥረት ያለባቸውን የኮሮና ቫይረስን ከመከላከል ጋር ተያይዞ ድጋፉ የሚቀጥል ከሆነ ችግሩ ብዙም አይስተዋልም፡፡
ሌላው የአለም የጤና ድርጅት ለንባብ ያቀረበው ከቤተሰብ እቅድ ዘዴ አገልግሎት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎች መኖራቸውንና ለእነሱም የሰጠውን መልስ የሚመለከት ነው፡፡ ሁለት ጥያቄዎችንና መልሶችን እነሆ…
1/ የ COVID-19 ወረርሽኝ ታማሚ በምንሆንበት ወቅት ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከያ መጠቀም ይቻላልን?
ማንኛውም በባለሙያ የሚታዘዝ ዘመናዊ የመከላከያ ዘዴን የኮሮና ቫይረስ ታማሚ በሚሆኑበት ወቅት ማቋረጥ አይገባም፡፡ ልክ እንደወትሮው መጠቀም ይቻላል፡፡ በእርግጥ ልጅ ከወለዱ ገና ስድስት ወር ገደማ ከሆነ እና አንዳንድ ሕመሞች ማለትም የስኩዋር ሕመም፤ከፍተኛ የሆነ የደም ግፊት፤ የጡት ካንሰር፤የመሳሰሉት ሕመሞች ታማሚ ከሆኑ ወይንም የሚያጨሱ ከሆነ ከሕክምና ባለሙያዎች ምክር መጠየቅ ተገቢ ይሆናል፡፡ ከባለሙያዎቹም ከጤና ጋር በማይ ጋጭ መልኩ የትኛውን መከላከያ መውሰድ ጠቃሚ ይሆናል የሚለውን ምክር ማግኘት ይቻላል፡፡
2/ የኮሮና ቫይረስ ታማሚ በምንሆንበት ጊዜ እርግዝና እንዳይኖረኝ እፈልጋለሁ፡፡ ምን ማድረግ አለብኝ?
እርግዝና እንዳይኖር በሚፈለግበት ወቅት ይወስዱት የነበረውን መከላከያ ምንጊዜም ሳያቋርጡ ወይንም እንደአዲስ በመጀመር መከላከያውን መውሰድ ጠቃሚ ነው፡፡ ለማንኛውም ለሚወስዱት እርምጃ ከጤና ተቋማት ወይንም ባለሙያዎች የምክር አገልግሎት ማግኘት እና በቂ መረጃ እንዲኖርዎ ማድረግ ጠቃሚ ነው፡፡ ለዚህም የግድ ወደተቋማቱ መሄድ ሳይጠበቅብዎ በስልክ አማካኝነት በመጠቀም ተገቢ የሆነውን ባለሙያ ማነጋገር ይጠቅማል፡፡ ይህንን ዘዴ መጠቀም የማይችሉ ከሆነ ግን በራስዎ ካለሐኪም መድሀኒት ማዘዣ የሚጠቀሙበትን ኮንዶም የመሳሰ ሉትን መከላከያዎች በቅርብዎ ከሚገኙ የመድሀኒት ቤቶች በመግዛት መጠቀም ይቻላል፡፡
በስተመጨረሻም ለትውስታ የምንለው የኢትዮጵያ የማህጸንና ጽንስ ሐኪሞች ማህበር ESOG የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ከሚያስ ችሉት ዘዴዎች መካከል የአፍና አፍንጫ መሸፈኛን (Face Mask) ከኢትዮጵያ ውጭ አስመ ጥቶ ማከፋፈሉን ነው። ማህበሩ (ESOG) ግንቦት 29/2012 በአዲስ አበባ ለሚገኙት ሚሽነሪስ ኦፍ ቻሪቲ (ማሪያ ቴሬዛ)፤ ጎጆ (የህሙማን ማረፊያ)፤ የወደ ቁትን አንሱ የነዳያን መርጃ ማህበር፤ ለተሰኙት ድርጅቶች በግንባር በመቅረብ ለእያንዳንዳቸው እስከ አራትሺህ የሚደርስ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን በስነስርአቱም ላይ የኢትዮጵያ የማህጸንና ጽንስ ሐኪሞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ የማህበሩ አባል የሆኑት ዶ/ር መንግስቱ ኃይለማርያም እና የማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሰላማዊት ክፍሌ ተገኝ ተው ነበር፡፡ ማህበሩ ድጋፍ ያደረገውን (Face Mask) ያገኘው በውጭ ከሚገኙ የሙያ አጋሮች በተደረገ ድጋፍ መሆኑ ታውቆአል፡፡




Read 9340 times