Saturday, 26 September 2020 00:00

የአንጋፋዋ አርቲስት ስርዓተ ቀብር ዛሬ ይፈፀማል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በተለያዩ የቲያትርና ፊልም ትወናዎቿ፤ ማስታወቂያ ስራዎች የምትታወቀው የአንጋፋዋ አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ስርዓተ ቀብር፣ በዛሬው እለት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ይፈፀማል።
በቲያትርና በፊልም፣ በተከታታይ የቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድራማዎች እንዲሁም በማስታወቂያ ስራዎች በእጅጉ የምትታወቀው   አንጋፋዋ  አርቲስት አልማዝ ኃይሌ፣ ባደረባት ህመም በትላንትናው እለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
ከአራት አሰርት አመታት በፊት በብሔራዊ ቲያትር በተወዛዋዥነት የተቀጠረችው አርቲስቷ፣ በኋላ ላይ ወደ ትወና እንደገባችና ጡረታ እስከወጣችበት ጊዜ ድረስ በሙያው እንደዘለቀች ይታወቃል። ከቲያትር ቤቱ በጡረታ መውጣቷን ተከትሎም፣ በተለያዩ ፊልሞችና የቲቪና የሬዲዮ ድራማዎች ላይ ተውናለች።
በአርቲስት አልማዝ ኃይሌ ህልፈት የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል የተሰማውን ሃዘን ስንገልፅ ለቤተሰቦቿ መፅናናትን እንመኛሰን፡፡


Read 4167 times