የ70ዓመቷ የሶል ንግስት አሪታ ፍራንክሊን እጅግ በማከብረው የአሜሪካን አይዶል ፕሮግራም ላይ በዳኝነት ብሰራ ደስ ይለኛል ብላ ለሲኤንኤን መናገሯም ትኩረት ስቧል፡፡የማርያ ኬሪ ባል የሆነውና የአሜሪካ ጎት ታለንት አስተዋዋቂ ሆኖ የሚሰራው ኒክ ካነን የአሜሪካን አይዶል ሃላፊዎች ባለቤቴን ለመቅጠር መፈለጋቸው ደስ ቢልም ክፍያዋን መቻላቸው ያጠራጥረኛል የሚል አስተያየት ሰጥቷል፡፡ ለጄኒፈር ሎፔዝ 20 ሚሊዮን ዶላር መክፈላቸውን እንደሚያውቅ የገለፀው ኒክ ካነን ማርያ ኬሪ እጥፍ ሊከፈላት ይገባልም እያለ ነው፡፡ ከወራት በፊት በተጠናቀቀው 11ኛው የአሜሪካን አይዶል በውድድሩ ታሪክ ዝቅተኛው ተመልካች መመዝገቡን ያስታወሰው ቺካጎ ትሪቡን በፕሮግራሙ ላይ በመስራችነት ከነበሩት የቀረው ማነጀሩና ፕሮዲውሰሩ ራንዲ ጃክሰን ብቻ መሆኑን ገልፆ በውድድሩ ላይ ዳኞች በቋሚነት አለመቀጠላቸው ለነበረው ስኬት ጋሬጣ ይሆናል ብሏል፡፡