Monday, 07 September 2020 00:00

ጎግል ለሰራተኞቹ አዲስ ከተማ ሊቆረቁር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ታዋቂው የአለማችን የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጎግል ለሰራተኞቹ ብቻ የሚፈቀድና 40 ሄክታር ስፋት ያለው አዲስ ከተማ በካሊፎርኒያ አቅራቢያ ሊቆረቁር ማቀዱን ባለፈው ማክሰኞ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ሚድልፊልድ ፓርክ የተባለ ስያሜ ያለው ይህ አዲስ ከተማ፣ ደረጃውን የጠበቀ መኖሪያ ቤት፣ መደብር፣ ፓርክና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራን ጨምሮ አንድ ከተማ ሊያሟላቸው የሚገባቸው መሰረተ ልማቶች እንደሚሟሉለት መነገሩንም ቴክራዳር ድረገጽ ዘግቧል፡፡
በአዲሱ የጎግል ከተማ 1.33 ሚሊዮን ስኩየር ጫማ ስፋት ያላቸው ቢሮዎችና እስከ 1ሺህ 850 የሚደርሱ የሰራተኞች የመኖሪያ ቤቶች እንደሚገነቡበት የጠቆመው ዘገባው፤ ኩባንያው ከተማውን ለመቆርቆር የወሰነው ሰራተኞቹ ዘና ብለው በነጻነት ስራቸውን እንዲያከናውኑ በማሰብ መሆኑንም አክሎ ገልጧል፡፡
ኩባንያው የከተማውን ዲዛይን በማሰራት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፣ ተቀማጭነቱ በአውስትራሊያ ከሆነው ሌንድሬዝ ከተባለ የሪልስቴት ኩባንያ ጋር የሚከናወነው የከተማዋ ግንባታ ስራ በምን ያህል ጊዜ እንደሚጠናቀቅ ይፋ የተደረገ መረጃ አለመኖሩን አመልክቷል፡፡

Read 2792 times Last modified on Saturday, 05 September 2020 13:18