Thursday, 13 August 2020 00:00

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ሞቅ ሲል ገዳይ፣ ቀዝቀዝ ሲል ዳኛ!
(አሌክስ አብርሃም)
በገጀራ የቆራረጠውን ሬሳ አጋድሞ አጠገቡ ግዳይ እንደጣለ አንበሳ እየተንጎማለለ ፎቶ ሲለጥፍ፣ የሰው ንብረት አውድሞ ሰልፊ እየተነሳ እዩኝ ሲል፣ በአደባባይ ህዝብን፣ ሐይማኖትን በፀያፍ ስድብ ሲያብጠለጥልና "ጨፍጭፏቸው ጨርሷቸው" ሲል፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት ይሄን ሁሉ በግልፅ ስናይ ‹‹ለሰላም ሲባል፣ ለአንድነት ሲባል›› እያለ አንገቱን ሲቀብር የነበረ ሁሉ ….ዛሬ የግፍ ግፍ የተፈፀመባቸው ያውም ጥቂቶቹ ሚዲያ ላይ ወጥተው ሀዘናቸውን ስለገለፁ ብቻ እንዲህ መበሳጨትና ኡኡ ማለት ምን ይሉታል? እየተባለ ያለው…. ተጠቂዎቹ ይሄው አሉ …አጥቂዎቹም ዛሬም እየፎከሩ አሉ ….ፍትህ ይከበር ነው እያልን ያለነው …
ፍትህ! የዛሬ መቶና ምናምን ዓመት ተፈፀመ ለሚሉት በደል ዘላለማቸውን የሚያለቅሱ ሰዎች፤ ከሶስት ሳምንት በፊት የተፈፀመ አሰቃቂ በደል ያውም ሚሊየን መረጃ ያለው እውነት አይናችንን ግንባር ያድርገው ብለው ለመካድ ሲፍገመገሙ ነው ያዘንነው!
ፍትህ ነው የምንለው … ነገም ድርጊቱን ከመደገም የሚያግድ ጠንካራ ዋስትና በክልሉ የለም ነው እያልን ያለነው ! ሞቅ ሲል ገዳይ፣ ቀዝቀዝ ሲል ዳኛ የሚሆን አመራር የሞላበት ክልል ውስጥ ብዙ ሺዎች አንገታቸው ላይ ገጀራ ተደቅኖባቸው ነው የሚኖሩት ነው የምንለው! ከዚህ በኋላ የአንድም ንፁህ ሰው ሞት ማየት አንፈልግም ነው የምንለው … ሌላ ምናልን?

Read 9622 times