Saturday, 08 August 2020 13:00

ሆን ብለው የሚያስሉ ኳስ ተጫዋቾች በቀይ ካርድ ሊባረሩ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በጨዋታ ላይ ሆነው ሳላቸው ሳይመጣባቸው ሆን ብለው በተቀናቃኝ ቡድን ተጫዋች ላይ ወይም በውድድር ሃላፊዎች ላይ የሚያስሉ የእግር ኳስ ተጫዋቾች በቀይ ካርድ ከሜዳ እንዲባረሩ በአለማቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሰሞኑ መወሰኑን ስካይ ስፖርትስ ድረገጽ ዘግቧል፡፡
ፌዴሬሽኑ ሆን ብለው የሚያስሉ ተጫዋቾች በቀይ ካርድ ከሜዳ እንዲወጡ የሚያስገድድ አዲስ ህግ ያወጣው የኮሮና ቫይረስን ስርጭት ለመግታት በማሰብ እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፣ ዳኞች ሆን ብለው በቅርብ ርቀት ከሚገኝ ተጫዋች ፊት የሚያስሉ ተጫዋቾችን በቀይ ካርድ እንዲያባርሩ መልዕክት ማስተላለፉንም አመልክቷል፡፡
ዳኞች ሳላቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው ተገቢውን ጥንቃቄ አድርገው የሚያስሉትን በቀይ ካርድ ከማባረር እንዲታቀቡ እንዲሁም ተጫዋቾች መሬት ላይ ምራቃቸውን እንዳይተፉ እንዲመክሩም ፌዴሬሽኑ ያወጣው አዲስ ህግ ያዝዛል፡፡

Read 1877 times